Jan 2025

ብሔራዊ የንፁህ ምግብ ማብሰያ ቴክኖሎጂ ፍኖተ ካርታ ትግበራ የአንድ አካል ኃላፊነት ብቻ አይደለም። ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ከ80% በላይ የሚሆነው የአገራችን ህዝብ የማገዶ እንጨት ተጠቃሚ በመሆኑ ለአካባቢ መራቆት፣ ለአፈር መሸርሸርና ለደን መጨፍጨፍ ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገ ከመሆኑም በላይ በተለይ ለህፃናትና ለሴቶች የቤት ውስጥ በካይ ጋዝ ተጋላጭነት እንዲኖር እያደረገና የታዳሽ ሀይል ልማትን ለሁሉም የማ

በኦሮሚያና በአማራ ክልል የመጠጥ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮና ግንባታ ውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በኦሮሚያና በአማራ ብሔራዋ ክልሎች ያለውን የውሃ ችግር የሚረዱና ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር በሀገራችን የተለያዩ ቦታዎች የሰሩና ልምድ ያካበቱ በመሆናቸው የጥልቅ የውሃ ጉድጓድ ቆፋሮው እንዲሁም የመጠጥ ውሃ ግንባታው በታቀደለት ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅ የኦሮሚያና የአማራ ክልል

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ህብረት አዲሱን የጀርመን አምባሳደር ተቀብለው አነጋገሩ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ህብረት አዲሱን የጀርመን አምባሳደር ሚ/ር ሀንስ ሀንፊልድን ተቀብለው ኢትዮጵያ ንጹህ አረንጓዴ ኢነርጂ በማምረት፤ ቀጠናውን በሃይል ለማተሳሰር እየሰራች መሆኑን አንስተው፤ እየተከናወነ የሚገኘው ምስራቅ አፍሪካን በሃየል የማስተሳሰር ተግባር ውጤታማ ነው ብለዋል፡፡

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት የግድብ ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ የሀብት ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር አካሄደ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ ፕሮጀክቱ አሁን ለደረሰበት ደረጃ ኢትየጵያዊያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ያላሰለሰ ድጋፍ ማድረጋቸውን በመግለጽ በዚህ የንቅናቄ መድረክ ተሳታፊዎች የህዳሴ ግድብ ቦንድ ገዝተው የማያውቁ አዳዲስ የፋይናንስ ተቋማት የቦንድ ግዥ እንዲፈጽሙ በማድረግ እስከ 60 ሚሊዮን

ከ298 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ባለብዙ መንደር የመጠጥ የውሃ ግንባታ የውል ስምምነት ተፈረመ፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ውሉን የሚፈርሙት ኮንትራክተሮች በሀገራችን የተለያዩ ቦታዎች የሰሩና ልምድ ያካበቱ በመሆናቸው ጠቅሰው፤ በሶማሌ ክልል ጉራዳሞሌ ወረዳ እንደሚገነባና አካባቢዎቹ ምንም አይነት የውሃ መሰረተ ልማት የተሰራላቸው ባለመኖሩ እንዲሁም ውሃ አጠር አካባቢ በመሆኑ ውሉን የወሰደው ድርጅት በ

የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ የበዓል መዋያ ድጋፍ ተደረገ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሚኒስትር ጽ/ቤት ኃለፊ አቶ ማሙሻ ሀይሉ በዓልን በዚህ መልኩ ስናከብር ያለንን የማካፈል ባህላችን ለማስቀጠል በማሰብ ለአቅመ ደካሞች፣ አነስተኛ ገቢ ላላቸው የሚኒስቴሩ ሰራተኞች፤ በተለይም በጸጥታው ዘርፍ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ለሰላም የቆሙ የጸጥታ አካላት አብረናችሁ ከጎናችሁ መሆናችንን ለ

የቤዚን ሞኒተሪንግ ስትራቴጂ ሰነድ ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡

ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ ሰነዱ በውስጥ አቅም ተዘጋጅቶ መቅረቡ አበረታች መሆኑን ገልፀው፤ ሰነዱ በአግባቡ ዳብሮ ለውሳኔ እንዲያመች እንዴት እና ከማን ጋር ይተገበራሉ የሚሉ ጉዳዮች ጭምር አንስተው በሰነዱ ላይ መጨመር እና መስተካከል አለበት ያሉትን አስተያየት ሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ ጎርፍ መከላከል ፕሮጀክት ውጤት እያስገኘ መሆኑ ተገለጸ።

ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ ከአለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ባሳለፍነው ክረምት ወቅት በአዋሽ ወንዝ ላይ የተሰራው የአስቸኳይ ጊዜ የቅድመ-ጎርፍ መከላከል ስራ ይከሰት የነበረውን ጉዳት በእጅጉ መቀነሱን አብራርተዋል። በላይኛው፣ በመካከለኛውና በታችኛው አዋሽ ላይ 151 ኪ.ሜ ዳይክ የተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ክቡር ሚኒስትሩ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ህብረት የእሰራኤል አምባሳደር ጋር ተወያዩ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ላይ የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ እና የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ላይ በርካታ የትብብር መስኮች መኖራቸውን አንስተው፤ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ላይ የፍሳሽ ውሃ የማጣራትና አጠቃቀም ላይ፤ የከርሰ ምድር ውሃ ቁፋሮ ቴክኖሎጂ ላይ፤ እንዲሁም ከውሃ ሀብት አስ

2 ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን ጨምሮ፣ 17 የላብራቶሪ ዕቃዎችና 1 የባዮጋዝ ጀኔሬተር ድጋፍ ተደረገ።

በርክክቡ ላይ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የገጠር ኢነርጂ ቴክኖሎጂ ልማትና ሽግግር መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሀኑ ወልዱ ተገኝተው 12 ዓመታት የባዮጋዝ ፕሮጀክት በኔዘርላንድስ የልማት ድርጅት ድጋፍ ሲተገበር መቆየቱን ገልጸው፤ የእለቱ ድጋፎች ፕሮጀክቱ መጠናቀቁን ተከትለው የመጡ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡

የአዋሽ ቤዚን አስተዳደር ፅ/ቤት የተቋሙን ሰራተኞችና የአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚ የሚያደርግ የእትክልትና ፍራፍሬ ልማት እያካሄደ መሆኑ ተገለጸ፡፡

የአከባቢው ጥበቃን በዘላቂነት በሚያረጋግጥ መልኩ ኢኮኖሚያዊ ጠቃሜታ በላቸው የተለያዩ የፍራፍሬ አይነቶች እየለሙ መሆናቸውን በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአዋሽ ቤዚን አስተዳደር ፅ/ቤት ኃላፊው አቶ አደን አብዱ ገልጸዋል።

የባሮ አኮቦ የተፋሰስ እቅድ ማጠቃለያ ዙሪያ ውይይት እየተደረገ ነው።

የተቀናጀ ውሃ ሀብት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ የውሃ ሀብቶችን በተሟላ ሁኔታ ጥቅም ላይ ለማዋል በተቀናጀ አግባብ ስራዎች እየተሰሩ እንዳልሆነ ገልጸው ፤ በተለይ የውሃ ሀብቱ ላይ ደግሞ የሚኖረው ጫና ከፍተኛ በመሆኑ ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን ዘላቂ የሆነ የውሀ ሀብት አጠቃቀም እንዲኖር ለማስቻል የተፋሰስ እ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከአርባ ምንጭ ዩንቨርስቲ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡

የገጠር ኢነርጂ ቴክኖሎጂ ልማት ማስፋፊያ መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ብርሀኑ ወልዱ በስልጠና ፕሮግራሞች ክህሎት እና እውቀትን ለማሳደግ፣ በታዳሽ ኃይል ቴክኖሎጂ እድገት ማለትም በማይክሮ ሃይድሮ፣ ሃይድሮ ሶላር፣ ንፋስ ኃይል፣ ባዮማስ ላይ ያተኮሩ የጋራ ምርምሮችን ለማካሄድለ፤ እንዲሁም የአውቶሜሽን ስራዎችን በተመለከተ እ

ለሁለት ቀናት ለውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮች ሲሰጥ የቆየው ዘርፍ ተኮር የጸረ- ሙስነናና ስነምግባር ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡

የክቡር ሚኒስትሩ ልዩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ ሃላፊነት ላይ ያለን አመራሮች ሙስናን በመዋጋት ለቀጣዩ ትውልድ ከሙስና የጸዳ ሁኔታ ማመቻቸት አለብን: አመራሩ ዘርፉ ላይ የሚታየውን ተጋላጭነት በማስተካከል ንጹህ የመጠጥ ውሃ ተደራሽነትን ለማሳደግና የኢነርጂ አቅርቦትን ለማስፋፋት መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በቅንጅት ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረመ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከ2015ቱ የፓሪስ የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነት ቀድማ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰውን ተጽእኖ በመረዳት ለመቀነስ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂ በመንደፍ ተግባራዊ እያደረገች

"ስነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት" በሚል መርህ ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡

የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ በሀገራችን እየመጣ ያለውን ለውጥ በተጠናከረ ሁኔታ ለማስቀጠል የተጀመረውን ሙስናን የመከላከል ትግል በተሟላ የህዝብ ተሳትፎ ዳር ለማድረስ እንዲቻል የሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ስራ አስፈፃሚ ከፌዴራል የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጋር በጋ

Dec 2024

ከ335 ሚሊየን ብር በላይ ወጭ ተደርጎበት የተገነባው የዲላ ከተማ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በቅርቡ ተመርቆ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ተገለጸ፡፡

በም/ር/መስተዳድር ማዕረግ የዲላ ክላስተር አስተባባሪና የውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ የተከበሩ ኢ/ር አክሊሉ አዳኝ ውሃ ላይ የሚሰራው ስራ ሌሎች ልማቶችን በማሳለጥ በጤና ፣በትምህርት፣ በኢኮኖሚና በአጠቃላይ በልማቱ ዘርፍ የሚያሳድረው ተጽእኖ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው ይህን ታሳቢ በማድረግ እንደ ክልል በ14 ከተ

ኢትዮጵያ ያሏትን የውሃ ሃብቶች በአግባቡ ለመጠቀም የተፋሰሶች ከፍተኛ ምክር ቤት ማቋቋም አስፈላጊ መሆኑ ተገለጸ፡፡

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ማስፈጸሚያ የተፋሰሶች ከፍተኛ ምክር ቤት ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጁ የውሃ ሀብታችንን አጠቃቀም ፍትሃዊነት ለመጠበቅና የሚወሰኑ ውሳኔዎች የሁሉም አካላት ጋራ ውሳኔ እንዲሆን ታሳቢ ተደርጎ መዘጋጀቱ ተገልጿል። የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ማስፈጸሚያ የተፋሰሶች ከፍተኛ ም/ቤት ረቂቅ አዋ

የተቀናጀ ውሃ ሀብት አስተዳደር ማስፈጸሚያ የተፋሰሶች ከፍተኛ ምክር ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ ላይ እና የውሃ አካል ዳርቻ ርቀት አወሳሰን፣ ልማት እና እንክብካቤ ረቂቅ አዋጆች ላይ ውይይት ተካሄደ።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ ኢትዮጵያ ያሏትን የውሃ ሃብቶች በአግባቡ ለመጠቀም በምታደርገው ጥረት ውስጥ የውሃ አካላት በተለያዩ ምክንያቶች ጉዳት እየደረሰባቸውና የውሃ አካላቱ እየተበከሉ መጠናቸውም እየቀነሰ እንደሆነ አውስተው፤ አሁን ላይ ወቅቱን የዋጀ ረቂቅ አዋጅ በመሆኑ

ሴቶችና ህፃናት በጭስ ምክንያት ይደርስብን የነበረውን የጤና ችግር ይቀርፋል፡፡ የኦቦርሶ ከተማ ነዋሪዎች

የምስራቅ ቦረና ዞን አስተዳዳሪ አቶ አብዱረዛቅ ሁሴን መንግስት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ጥረት የኤሌክትሪክ መብራት ተደራሽ በማይሆንበት ቦታ እንደኦቦርሶ ከተማ ለመብራትና ለውሃ ማመንጫ የሚሆንና በአካባቢው የመጀመሪያው የሆነው የፀሀይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በገጠራማ አካባቢዎች ላይ ለማዳረስ

በ 195 ሚ ብር ወጪ 370 ኪሎ ዋት ማመንጨት የሚችል የሶላር ኃይል ማመንጫ ተመረቀ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ የተመራ ቡድን በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ቦረና ዞን መደወላቡ ወረዳ ኦቦርሶ ቀበሌ በኦዳ ሶላር ሚኒ ግሪድ ሳይት ላይ በተደረገው የምርቃት መርሃ ግብር ላይ ባስተላለፉት መልእክት 15 ሺ የገጠሩን ማህበረሰብ ንፁህ ኢነርጂ ተጠቃሚ ለማድረግ ተግባራዊ የሚደረገው ፕሮጀክት ለመብራት፣ ለማብሰያ፣

የምስራቅ አፍሪካ ኤሌክትሪክ ሀይዌይ (East Africa Electric Highway) ፕሮጀክት አካል የሆነው ኃይል ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የሚያስተላልፈው መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት ጀመረ፡፡

የምስራቅ አፍሪካ ኤሌክትሪክ ሀይዌይ ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር በኢትዮጵያና በኬንያ መካከል የተፈጠረ ሲሆን፤ ከኢትዮጵያ ወደ ኬንያ በተዘረጋው የኃይል አቅርቦት መሰረተልማት በኩል የኃይል ትስስሩ እውን ሆኗል፡፡

ከ 30 ሺ በላይ ቤተሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ሊገነባ ነው።

በክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን በቦሪቻ ወረዳ ከ 30 ሺ በላይ ቤተሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የቆራንጎጌ ሸንደሎልዎ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰምድር ውሃ ፕሮጀክት አንዱ ሲሆን በፕሮግራሙ 110 የመጠጥ ውሃ ተቋማት በ55 ወረዳዎች ተገንብተው የህብረተሰቡን ችግር ይ

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ የመሠረት ድንጋይ አስቀመጡ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ሀገራችን ኢትዮጵያ በውሃው ዘርፍ ትልቅ መዋእለ ንዋይ እያፈሰሰች እንደምትገኝና ንጽህናውን የጠበቀ ውሃ በማቅረብ የህብረተሰቡን የውሃ ችግር ከመፍታተት ባለፈ ንጽህናው በተጓደለ ውሃ ምክንያት የሚከሰቱ በሽታዎችን ለመከላከል ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ነው ብለዋል።  

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኃይል ልማት አጋሮች ጋር ተወያየ።

ፕሮግራሙን የመሩት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ ከ20 በላይ የኢነርጂ ልማት አጋሮች እንዳላቸውና በአመት ሁለት ጊዜ እየተገናኙ ኢነርጂን በሚመለከት መረጃ እንደሚለዋወጡም ገልጸዋል፡፡

የብሄራዊ ዋን ዋሽ ፕሮግራም የ2017 በጀት ዓመት 1ኛው ሩብ ዓመት አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ።

የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ መድረኩ ያለንበትን አፈፃፀምና ቀጣይ መሰራት ያለባችውን ያመላከተ መድረክ መሆኑን ጠቅሰው መንግስት ለህዝባችን ውሃ የማቅረብ ግዴታ ያለበት በመሆኑ ከልማት አጋሮቻችን ጋር የምንፈጽማቸውን ፕሮጀክቶችና ፕሮግራሞች በልዩ ትኩረት መምራት እንደሚያስፈልግ፣ የክትትልና ግምገማ

የተቆጣጣሪ ባለስልጣን ማቋቋም ወደ ሙሉ ትግበራ እንዲሸጋገር አቅጣጫ ተቀመጠ፡፡

በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክብር ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ሞቱማ መቃሳ እስከአሁን የመጣንበት የውሃና ሳኒቴሽን አቅርቦት እና አገልግሎት ውስንነቶች በዘላቂነት ለመፍታት ባለመቻሉ የከተማ የውሃና ሳኒቴሽን ተቆጣጣሪ አካል ማቋቋም አስፈላጊ መሆኑን ታምኖበታል ብለዋል።

የፀረ ኤች.አይ.ቪ /ኤድስ ቀንና የፀረ-ፆታዊ ጥቃት ቀንን ምክንያት በማድረግ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ።

የፀረ-ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ37ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ35ኛ ጊዜ "ሰብዓዊ መብትን ያከበረ የኤች አይ ቪ አገልግሎት ለሁሉም!" በሚል መሪ ቃል የተከበረ ሲሆን የፀረ-ፆታዊ ጥቃት ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ33ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ19ኛ ጊዜ "የሴቷ ጥቃት የኔም ነው፤ ዝም አልል

የከተማ የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ተቆጣጣሪ አካል ማቋቋም የአገልግሎት አሰጣጥ ደረጃዎችን ጠብቆ የተሳለጠ አገልግሎት ለመስጠት ወሳኝ ነው ተባለ።

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በውሃና ኢነርጂ ዘርፍ እንደሀገር የአሰራር ስርዓት ለመዘርጋት በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አንስተው፤ በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላይ የቀረቡት የውሃ አካል ዳርቻ አከላለል፣ ልማት እንክብካቤና አጠቃቀም ረቂቅ አዋጅና የ

የከተማ የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን አገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ ሰነድ ላይ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ታምሩ ገደፋ ከዚህ በፊት ስንገለገልበት የነበረውን የከተሞች መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን መመሪያ ማሻሻል በማስፈለጉና አሁን ላይ ብዙ አይነት ቴክኖሎጂዎች በመምጣታቸው፤ የፖሊሲ እና ጋይድ ላየን ለውጥ እየተከሰተ በመሆኑ የተሻሻለና ወጥ የሆነ የውሃ ጥራ

የቸክ ሪፐብሊክ ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ሚ/ር ማሪያን ዩሬስካ ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር በትብብር የሚሰሩ ስራዎችን ጎበኙ፡፡

ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ ቸክ እና ኢትዮጵያ ከ1980ዎቹ ጀምሮ በትብብር በርካታ ስራዎች እየሰሩ መሆኑን ገልጸው፤ በመልካ ዋከና የኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ ላይ ባለሙያዎችን በመላክ ፣ የሃይድሮሎጂ፣ የጂኦሎጂካል ፣ የአፈር እና የጂኦሎጂካል ስጋት ካርታዎች ላይ እና ውሃ ለሰዎች ፣ ለእርሻ እና ለኢንዱስትሪ የማዋል

በሀገራት መካከል የሚደረግ የሀይል ትስስር በየሀገራቱ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ መሰረታዊ ነው፡፡

በሞምባሳ፣ ኬኒያ እየተካሄደ በሚገኘው የምሥራቅ አፍሪካ የሃይል ትስስር (East African Power pool) የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በሀገራት መካከል የሚደረግ የሀይል ትስስር በየሀገራቱ ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ መሰረታዊ ነ

የከርሰምድር የውሃ ሀብትን በማልማት ለማስተዳደር የሚያስችሉ የጥናትና የማማከር ስራዎች በ132 ሚሊየን ብር ወጪ የውል ስምምነት ተፈረመ፡፡

የውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ ለሚኒስትር መስሪያ ቤታችን ከተሰጠን ሀላፊነት አንዱ ከውሃ ጋር ተያያዥ የሆኑ ሀብቶችን መቆጣጠርና መከታተል ነው፡፡ በዚህም የውሃ ሀብታችን ለመጠቀም እና ዘላቂነቱን ለማረጋገጥ ፖሊሲ በማዘጋጀት እና እስትራቴጂ በመንደፍ እየተተገበረ መሆኑን ገልጸ

በኢነርጂ ዘርፍ የተሰማሩ ሴቶችን አቅም ለማሳደግ የሁሉም ድጋፍ ያስፈልጋል። ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ የኢትዮጵያ ሴቶች ኢነርጂ ማህበር የአመቱን ተፅዕኖ ፈጣሪ ሴቶች እውቅና ለመስጠት በተዘጋጀው መድረክ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት በኢነርጂ ዘርፍ የተሰማሩ ሴቶችን አቅም ለማሳደግ የሁሉም ድጋፍ ያስፈልጋል ብለዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከበርን ማኑፋክቸሪግ ኢንዱስትሪ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል ውይይት አደረገ፡፡

የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ኢነርጂ ለማንኛውም የልማት እንቅስቃሴ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው ኢትዮጵያ የታዳሽ ኢነርጂ እምቅ ሀብት ባለቤት ብትሆንም የሀይል ተደራሽነት በሚፈለገው መጠን አላደገም፤ በተለይም ደግሞ የንጹህ ማብሰያ ቴክኖሎጅ የሚጠቀመው ህዝባችን ከ10 በመቶ የሚበልጥ አይደለ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከ6 ሚሊዬን ብር በላይ በሚሆን ወጪ የአቅም ግንባታ የኮንትራት የውል ስምምነት ተፈራረመ፡፡

በውሃና ኢነርጂ ሚኒሰቴር የገጠር ኢነርጂ ቴክኖሎጅ ልማትና ሽግግር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ብርሀኑ ወልዱ የውል ስምምነቱ የተፈረመው ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ጋር ሲሆን በአፍሪካ ቻይልድ ሚኒ ግሪድ ካሪኩለም ዝግጅትና የምህንድስና ትምህርት ላላቸው ግለሰቦች ሚኒግሪድን በተመለከተ ስልጠና መስጠትን

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከ182 ሚሊዬን በላይ በሚሆን ብር 6 የጥልቅ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮና ግንባታ የኮንትራት የውል ስምምነት ተፈራረመ፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የውል ስምምነቱ የተፈረመው በኦሮሚያ ክልል በሁለት ዞኖች፤ አንደኛው ሶስት ጥልቅ የውሃ ጉድጓዶች በጉጂ ዞን በአበያ ወረዳ በዋተማ ቢዮ ማገጫ ሳይት ሲሆን፤ ሀለተኛውና ቀሪዎቹ 3ቱ ጥልቅ የውሃ ጉድጓዶች በጂማ ዞን በቀርሳ ወረዳ በኩሳዬ ቢሮሌ እና ካራ ጎራ ሳይቶች እንደሚገነባ ገ

19ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል "አገራዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል ተከበረ።

በዓሉን አስመልክቶ ንግግር ያደረጉት የክቡር ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ማሙሻ ሀይሉ የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የእኩልነትና የመብት ጥያቄ ሕጋዊ ማዕቀፍ ይዞ ከተመለሰና ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ከህዳር 1987 ጀምሮ ብዙ ዓመታትን አስቆጥሯል ካሉ በኋላ በዓሉ ከ1998 ጀምሮ በመላው ኢትዮጽያ በተለያዩ የብሔር ብሔረሰ

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የእስያ መሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ ፕሬዚዳንት እና የቦርዱ ሊቀመንበር ሚስተር ጂን ሊኩንን ተቀብለው አነጋገሩ።

ክቡር ሚኒስትሩ በውይይቱ ወቅት የውሃ ሀይል ማመንጫ ግድቦች እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና የኮይሻ የውሃ ሀይል ማመንጫ ግድብ ላይ ጥሩ ተሞክሮ እንዳለ አንስተው የኃይል ማመንጫ መሰረተ ልማቶች ላይ ስኬታማ ለመሆንና ቀሪውን የህብረተሰብ ክፍል ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ዘመናዊ የአሰሰራ ስርአት ላይ እገዛ

የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አመራሮች ቡድን "ኢትዮ -ግሪን ሞቢሊቲ 2024" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀውን አለም አቀፍ ኤግዚቢሽንና ሲምፖዚየም ጎበኙ፡፡

በክቡር ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማሙሻ ሀይሉ የተመራ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አመራሮች ቡድን የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በሁዋጂያን ኢንተርናሽናል ቀላል ኢንዱስትሪ ፓርክ "ኢትዮ -ግሪን ሞቢሊቲ 2024" በሚል መሪ ቃል ያዘጋጀውን አለም አቀፍ ኤግዚቢሽንና ሲምፖዚየም ጎበኙ፡፡

Nov 2024

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ እየተገነባ የሚገኘውን የባዮ ጋዝ ፕሮጀክት ጎበኙ፡፡

ክቡር ሚኒስትር ዲኤታው በቦታው ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ ሀገራችን ካላት የታዳሽ ሀይል አንዱ የባዮ ጋዝ ኢነርጂ መሆኑን ገልጸው፤ እንደሀገር በአባወራ ደረጃ መጠቀም ከጀመርን የቆየን ቢሆንም አሁን ላይ በሀገራችን የመጀመሪያ ትለቁ ከመሬት በላይ የተተከለና ዳጀስተሩ 300 ሜትር ኪዩብ ካፓሲቲ ያለው የባዮ ጋዝ ምርት

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከጣሊያን መንግስት የልማት ትብብር ድርጅት ጋር የትብብር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡

ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ እና የጣሊያን የልማት ትብብር ድርጅት ተወካይ ሀላፊ ሚስ. አሌሳንድራ አቲሳኒ ሲሆኑ፤ ክቡር ሚኒስተር ዴኤታው የውል ስምምነቱ በዋናነት በሶስት ተፋሰሶች በአዋሽ፣ በዋቢ ሸበሌ እና በደናክል ተፋሰሶች ላይ የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ስርዓትን ለማስፈን በትብብር ለማልማትና ለማመቻቸት መሆ

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የጣሊያን የውጭ ጉዳይና አለም አቀፍ ትብብር ምክትል ሚኒስትር ሚ/ር ጆርጅዮ ሲሊን ተቀብለው አነጋገሩ፡፡

ክቡር ሚኒስትሩ በነበራቸው ቆይታ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በሶስት ዋና ዋና ዘርፎች ላይ ትኩረቱን አድርጎ እየሰራ መሆኑን፤ ማለትም በውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ የውሃ ሀብትን በማልማት በመንከባከብና በመጠቀም ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑንና በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍም በተመሳሳይ በተለያዩ ፕሮግራሞች የመጠጥ

የሶላር ሀይል መስኖ ፕሮጀክቱ ከግብርና ልማት ባሻገር ማህበራዊ ችግራችንን ይፈታል===========የሀዋሳ ዙሪያ ነዋሪዎች።

አካባቢያቸው ውሃ አጠር በመሆኑና የዝናብ ዉሃን ብቻ በመጠቀም በአመት አንድ ጊዜ ያመርቱ እንደነበር ጠቁመው፤ በቂ ባለመሆኑ የኢኮኖሚ ችግር ውስጥ እንዳሉና ኑሯቸውን ለማሸነፍ ወደ አጎራባች ቀበሌ ሄደው የጉልበት ስራ እንደሚሰሩና ያላቸውን መሬት በመጠቀም በአመት ሶስት ጊዜ ለማምረት እንደሚችሉ; ድንች፣ ስንዴ፣ አኩሪ

በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ በ120 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባ የሶላር ፓምፕ መስኖ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በበኩላቸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ህብረተሰቡን ፍትሀዊ የልማት ተጠቃሚ ለማድረግ የዋና የኤሌክትሪክ መስመር በማይደርስባቸው አካባቢዎች የሶላር ኢነርጅ ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ሶላር መስኖ ፕሮጀክት አንዱ ማሳያ ነው ያሉት ክቡር ሚኒስትሩ ፕሮጀክቱ ረጅም እድሜ እን

ከ387 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የመጠጥ ውሃ ግንባታ ውል ስምምነት ተደረገ፡፡

ሰምምነቱን የተፈራረሙት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በሲዳማ ክልል ሀዋሳ ዙሪያ ባለብዙ መንደር የንፁህ መጠጥ ውሃ ግንባታ ከጃርሶ የውሃ ስራዎች ኮንስትራክሽን በ387 ብር በላይ ወጪ በማድረግ በ15 ወራት የሚጠናቀቅ የግንባታ የውል ስም

የአለም የእጅ መታጠብ እና የመፀዳጃ ቤት ቀን ተከበረ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በመድረኩ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር የንፁህ ውሃ አቅርቦት፣ የሳኒቴሽን አገልግሎት እና የንፅህና አጠባበቅ ለሰው ልጅ መሰረታዊ መሆናቸውን ገልፀው፤ ሳንቴሽን የመፀዳጃ ቤት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የጤናና የልማት ጉዳይ ነው ብለዋል።

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በ40ኛ መደበኛ ስብሰባ የውሃ ሀብት አስተዳደርን ለማስፈን የሚያግዙ አዋጆችን በሙሉ ድምጽ በማጽደቅ ወደ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ ወስኗል፡፡

ምክር ቤቱ ውይይት ያደረገበት አንደኛው ረቂቅ አዋጅ የውሃ አካል ዳርቻ አከላለል፣ ልማት፣ እንክብካቤ እና አጠቃቀም ረቂቅ አዋጅ ነው፡፡ በሀገራችን በውሃ አካላት ዳርቻዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ጉዳት ለመከላከል እንዲቻል የውሃ አካላት ዳርቻ መከለልና በዘላቂነት ማልማት፣ መንከባከብና ጥበቃ ማድረግ የውሃ ስነ-ምህዳር

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ከቻይናው ዞንግዩንግ ኤሌክትሪክ ኢኩዩፕመንት ግሩፕ ጋር ተወያዩ፡፡

ኢትዮጵያ በሀይሉ ዘርፍ እንደ ኬኒያ፣ ታንዛኒያ፣ ጅቡቲና ሱዳን ላሉ ጎረቤት ሀገሮች ሀይል እያቀረበች እንደምትገኝ የገለጹት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው ሀይል የማስተላለፍና የማሰራጨት ስራ ሲሰራ የኬብል፣ የከፍተኛ፣ የመካከለኛና የዝቅተኛ ቮልቴጅ ችግር መኖሩ የሀይል መቆራረጥ ችግር ማስከተሉንና ለዚህ ደግሞ የትራንስፎርመር

ክቡር ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ጋር ተወያዩ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የጣሊያን ድርጅቶች በውሃ ሀይል ማመንጫ ግድቦች ግንባታ ላይ በተለይ፤ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ የውሃ ሀይል ማመንጫ ግድብና የኮይሻ የውሃ ሀይል ማመንጫ ግድብ ላይ ከፍተኛ ተሳትፎ እያደረጉ እንደሚገኙ ገልጸው፤ በሀይል ማመንጫ ግንባታ ከመሳተፍ ባሻገር የጣሊያን መንግስት በውሃ ሀብት አ