Feb 2026

በተለያዩ አምዶች ተከፋፍሎ በተዘገጀው የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎረም ስልጠና ተሰጠ።

የስልጠናውን መርሃግብር የማስጀመሪያ ንግግር ያደረጉት የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የአብይ ኮሚቴ ፀሐፊ አቶ ኦልቀባ ባሼ የሪፎርሙ ትልቁ አላማ ብቃትን ከሪፎረም ተግባራት ጋር በማገናኘት በተቋሙ የሚጠበቀውን ውጤት ለማምጣት ነው ብለዋል።

ክቡር ሚኒስትሩ ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ልኡክ ጋር በትብብር ለመስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መከሩ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ልኡክ ጋር በትብብር ለመስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል። በነበራቸው ቆይታ ልኡካኑ ላነሷቸው ጥያቄዎችም ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በምእራብ ሃረርጌ ዞን ቡርቃ ዲምቱ ወረዳ የሃሮ ጉራቲ እና የቡርቃ ኦዳ ሶላር ሚኒ ግሪድ ፕሮጀክት ታሪክ የቀየረ በጨለማ የተገኘ ብርሀን መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ኤሌክትሪፍኬሽን ዘርፍ የአደሌ ፕሮጀክት እና የአፍሪካ ልማት ባንክ አስተባባሪ አቶ አዲስ ዓለም መብራቱ የኤሌክትሪ ፍኬሽን የተያዘውን እቅድ ለማሳካት በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸው በአፍሪካ ልማት ባንክ የገንዘብ ድጋፍ 25 ሚኒ ግሪድ ፕሮጀክቶችን በመገንባት በጣም ገጠራማ አካባቢ ያሉ የ

የአፍሪካ የኢኮሶክ ምክር ቤት /ECOSOCC-Economic Social & Cultural Council/ዓመታዊ ስብሰባ እየተካሄደ ነው።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በመድረኩ ተገኝተው በመወያያ አጀንደ ዙሪያና በአጠቃላይ እንደሀገር ኢትዮጵያ በዘርፉ ያሳካችውን ስኬቶች ፣በመጡ ለውጦችና በአፍሪካ ደረጃ እንዴት ተቀናጅተን በህብረትና በትብብር መስራት አለብን በሚሉ ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ንግግር አድርገዋል።

የአካባቢውን ማህበረሰብ የመብራት ጥያቄ የሚመልሰው ፕሮጀክት አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

በዓለም ባንክና በኢትዮጵያ መንግስት ወጪ የተገነባውን ፕሮጀክት በይፋ ያስጀመሩት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ በሃሮ ጉራቲ 210 ኪሎ ዋት እና በቡርቃ ኦዳ 132 ኪሎ ዋት የሚያመነጨው የፀኃይ ሀይል ፕሮጀክት የአካባቢውን ማህበረሰብ የዘመናት የመብራት

ፕሮጀክቱ ለዘመናት የቆዬ ችግራቸውን እንደሚፈታላቸው ገለጹ።

የውሀና ኢነርጅ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በመተባበር በኦሮሚያ ክልል የምእራብ አርሲ ዞን ናንሰቦ ወረዳ የተገነባው የጸሀይ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ለዘመናት የቆዬ ችግራቸውን እንደፈታላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።

በፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች የገጠር ከተሞችንና መንደሮችን የኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው።ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን የነንሰቦ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት /Solar Mini-grid Project/ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑን ያበሰሩት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው በተቋሙ ከዋናው የኤሌክትሪክ መስመር ርቀው የሚኖሩ የገጠር ማህበረሰብ ክፍሎችን የኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ ከአጋር አካላት ጋር በቅንጅት እየተ

የነጻና ገለልተኛና የብዝሃነትና አካታችነት ሲቪል ሰርቪስ ግንባታ አምድ ላይ ስልጠና ተሰጠ።

የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ኦልቀባ ባሼ በለፉት ስድስት ወራት የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርምን ውጤታማ ለማድረግ በርካታ የቅድመ ዝግጅት ሰራዎች መሠራታቸውን ገልጸው በሀገራችን የሲቪል ሰርቪስ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምእራፍ ለመጀመር በታለመው መጠነ ሰፊ የሪፎርም ጉዞ ላይ በመወያየት ግንዛቤ ለመያዝ

የኢትዮጵያ ጀርመን ኢነርጂ ትብብር አውደ ጥናት መድረክ ተካሄደ፡፡

የኢነርጂ ሃብት ጥናት መሪ ስራ አስፈጻሚ የመርሃግብሩን ይዘት በተመለከተ እንዳስገነዘቡት ኢትዮጵያ ሃገራችን ታዳሽ ኢነርጂን አስመልክቶ እምቅ ሃብት እንዳላትና ይህንን እምቅ ሃብት ለልማቱ በሚያመች ሁኔታ ተግባራዊ ለማድረግ የአረንጓዴ ሃይድሮጂ ቴክኖሎጂን ጥቅም ላይ በማዋል ኢንቨስትመንትን ለማሳለጥ የሚያስችል አውደ ጥ

የፍሳሽ ማጣሪያ ፕሮጀክቶች( Faecal Sludge Treatment Plant) ተገንብተው ዘላቂ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

የሳኒቴሽን መሠረተ ልማት መሪ ሰራ አስፈጻሚ አቶ ኑረዲን ሙሃመድ በሁለተኛው የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት በርካታ ሰራዎች መከናወናቸውን ገልጸው በተለይም ለሳኒቴሽን መሠረተ ልማት በተሰጠው ትኩረት በርካታ መዋለ ንዋይ ፈሶባቸው የተገነቡ ፕሮጀክቶች ዘላቂ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ ወሳኝ ነው ብለዋል።

የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ በመሆናችን ደስተኛ ነን። ===የሉኮ አባያ ዙሪያ የመሬራ ቀበሌ ነዋሪዎች

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በጋራ ያስገነባውን የመሬራ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ለአገልግሎት ይፋ ባደረገበት መርሃግብር ላይ ያነጋገርናቸው የአካባቢው ነዋሪዎች በፕሮጀክቱ ተጠቃሚ መሆናቸው እንዳስደሰታቸው ገለፁ።

ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የመረራ ሶላር ሚኒ ግሪድ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን በፍትኃዊነት ለሁሉም ማህብረሰብ እንዲዳረስ የመከታተልና የመተግበር ኃላፊነት ያለው መሆኑን ጠቅሰው፤ በዚህ ፕሮጀክትም ከሚገኙት ኮምፖነንቶች ማለትም በሶላር ሚኒ ግሪድ ፕሮጀክቶች በትምህርትና እና የጤና ተቋማት የቤተሰብ የሶላር

ኢትዮጵያ ለታላቁ የህዳሴ ግድብ አንድም ብር ብድርና ዕርዳታ አልወሰደችም፡፡ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ ታላቁ የሕዳሴ ግድባችን በጀግኖች ኢትዮጵያውያን ቁርጠኛ አቋም ተገንብቶ የተጠናቀቀ ነውም ብለዋል፡፡

የአዋሽ ተፋሰስ አስተዳደር ፅህፈት ቤት በውሃ ምደባ ማህበራዊ አካታችነት ላይ ትኩረት ያደረገ የጥናት ሰነድ ግኝት የግምገማ መድረክ ተካሄደ፡፡

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ስራ አስፈፃሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለጹት በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በሚገኙ ዋና ዋና ዘርፎች መካከል የተፋሰስ አስተዳደር ዘርፍ በሃገራችን ያለው ውሃ ዘላቂ በሆነ መንገድ ጥቅም ላይ የሚውልበትን አግባብ የሚወስን ዘርፍ በመሆኑ ትልቅ ትኩረት የሚሻ ነው ያሉ ሲሆን

የተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ አስተዳደር መረጃ አያያዝ ስርዓት /ICSMIS/ አጠቃቀምና አተገባበር ላይ ስልጠና ተሰጠ፡፡

የሰው ሀብት ልማት አስተዳደር ስራ አስፈፃሚ አቶ መለሰ መንግስቱ የICSMIS ስልጠና ከዚህ በፊት ለባለሞያዎች በየደረጃው መሰጠቱን አስታውሰው፤ አመራሩ የግሉን መረጃ ለማየት፣ ከሰው ሃብት የሚፈለጉ አገልግሎቶችን ለማግኘትና በስራቸው ያሉትን የባለሞያዎችን ፍቃድ እንዴት ማፅደቅ ይቻላል የሚለውን የሚያስረዳ በመሆኑ ግል

Jan 2026

ባለፋት አመታት ዘርፉ ባከናወናቸው ተግባራት ውጤታማ ስራ መስራቱ ተገለጸ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ ሀገራችን ያላትን ሃብት በአግባቡ መጠቀምና መጠበቅ የሚያስችል በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ገልጸው በውሃ ሃብት አስተዳደር ዘርፍ የውሃ ሀብት እንዳይበከል የውሃ አካላት ዳርቻ ጥበቃ አዋጅ አጸድቀናል፣ በአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር እንደሀገር ከ48ቢሊየን በላይ ችግኝ ተክለናል፣

የስርዓተ ጾታና ኢነርጂ ቴክኒካል የስራ ቡድን ውይይት አካሄደ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ትግበራ ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ የውብ ዳር አሚኖ የኢነርጂ ስራዎች በተቀናጀ መንገድ መሬት ላይ ወርደው የህብረተሰቡ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በእውቀት፣ በገንዘብ እና በሀሳብ በመደጋገፍ ውጤታማ ስራ ለመስራት የሚቻልበት የስራ ቡድን ነው ብለዋል።

በልማት ስራዎች ጉብኝት፣በ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና በተለያዩ ጉዳዮች ግንዛቤ በመፍጠር ሲካሄድ የነበረ መርሃግብር ዛሬ ተጠቃለለ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የሁሉም ክልል የውሃና ኢነርጂ ቢሮ የ6ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት መቅረቡ አንዱ ክልል ከሌላው ክልል መልካምና ምርጥ ተሞክሮዎችን በመቀመር ልምድ በመለዋወጥ ሁሉም ወደተሻለ አፈፃፀም ደረጃ እንዲደርስ ስለሚያግዝ ነው ብለዋል።

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ላይ ስልጠና ተሰጠ::

የስራ አመራር ዋና ሰራ አስፈጻሚ እና የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የአብይ ኮሚቴ አባልና ጸሀፊ አቶ ኦልቀባ ባሼ መንግስት ለዜጎች የሚሰጠው አገልግሎትና የሚመራበት ቢሮክራሲያዊ ሂደት የሀገር ህልውና በመሆኑ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓትንና ሂደቶችን በማሻሻል የሚፈለገውን ውጤት ለማምጣት ሪፎርሙ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የ2018 ዓ/ም የ6 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም በነቀምት ከተማ እየተገመገመ ነው።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በየበጀት ዓመቱ ሁለት ጊዜ በተለያዩ ክልሎች የሚደረገው የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማና ውይይት መድረከ ውጤቶቻችንን ከፍ ለማድረግ ከማገዝ ባሻገር ባህሎቻችንንና መልካም ተሞክሮዎችን በመለዋወጥ ህብረብሔራዊ አንድነትንና ቅንጅታዊ አሰራርን ይፈጥራል ብለዋል።

የደንበል ሀይቅን ከእንቦጭ አረም ለመታደግ የሁሉም ህብረተሰብ ሀላፊነት መሆኑ ተገለጸ።

"መጤ የእንቦጭ አረምን ከደንበል ሃይቅ ላይበጋራ እናስወግድ!! "በሚል መሪ ቃል የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ልማት ጽ/ቤት ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ባቱ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በጋራ በተዘጋጀው የህብረተሰብ ንቅናቄ ላይ የደንበል ሀይቅን መጠበቅ የሁሉም ህብረተሰብ ሀላፊነት መሆኑ ተገለጸ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮዎችና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት እቅድ አፈጻጸምን እየገመገመ ነው።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ አፈጻጸማችን በየጊዜው በተለያዩ የሀገራችን ከተሞች እየተዘዋወርን ስንገመግም ትልቅ የሆነን የውሃ ሀብት የምንመራና የምናስተዳድር እንደመሆናችን አንዳችን ከሌላችን ተሞክሮን በመውሰድ በዘርፉ የተሻለ ሰራ ለመስራት ስለሚያስችለን ነው ብለዋል።

በክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የተመራ ቡድን የነቀምቴ አካባቢ የልማት ስራዎችን ገበኙ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የተመራ ቡድን በነቀምቴ አካባቢ እየተገነባ ያለውን ዘመናዊ የፍሳሽ ማጣሪያ ፕሮጀክት ፣ 274 ሺ የከተማውንና አካባቢውን ማህበረሰብ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ እያደረገ ያለውን የጫንጮ ግድብ እና የውሃ ትሪትመንት ማእከል እየሰጠ ያለውን አገልግሎት ተመልክተዋል።

ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ በሐይደሮሎጂና ተፋሰስ መረጃ አስተዳደር መሪ ስራ አሰፈፃሚ እየተዘጋጁ ያሉ ሰነዶችን ገመገሙ፡፡

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስተሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞተማ መቃሳ በሐይደሮሎጂና ተፋሰስ መረጃ አስተዳደር መሪ ስራ አሰፈፃሚ እየተዘጋጁ ያሉ ሰነዶችን ገምግመዋል።

የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት እቅድ አፈጻጸም እየተገመገመ ነው።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ መደረኩ ላለፉት ስድስት ወራት በየዘርፉ የተከናወኑ በርካታ ጠንካራ ስራዎችን የምናስቀጥልበትና በቀጣይ ትኩረት አድርገን የምንተገብራቸውን በጋራ በመገምገም የበለጠ ውጤታማ እንድንሆን የምንችልበትን ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው ብለዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከ115 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የማማከር ውል ስምምነት ፈጸመ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ስምምነቱ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከሚያከናውናቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት አንዱ የሆነው የሳኒቴሽን መሠረተ ልማት ግንባታ በከተሞች አካባቢ የተሳለጠ አገልግሎት በሚሰጡበት ደረጃ ለማድረስ ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ችግር ፈቺ ሊሆኑ ይገባል ተባለ።

በቤዚን አቀፍ ዘላቂነት ማረጋገጫ ፕሮጀክት (BaSRINET) በአዋሽ ቤዚን ያንጉዲ ካችመንት፣ በዋቢሸበሌ ቤዚን ኦሮሚያ ክልል ባቢሌ ወረዳ ኢፋዴን ካችመንት እና በሶማሌ ክልል ዋቢ ሸበሌ ዞን አሎኢገርሲ ካችመንት ላይ ለሚተገበረው የተፋሰስ ዕቅድ ዝግጅት ዙሪያ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና የማጠቃለያ መርሃግብር ላይ የአቅም

የውሃ ጥናትና ዲዛይን እንዲሁም የፕሮጀክቶችን ቀጣይነትን ለማረጋገጥ ከሚደግፉ አማካሪ ድርጅቶች ጋር ውል ተፈረመ።

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የውሃ ጥናትና ዲዛይን ስራዎችን ከሚያከናውን እና የፕሮጀክቶችን ቀጣይነትን ለማረጋገጥ ከሚደግፉ አማካሪ ድርጅቶች ጋር የውል ስምምነት አድርገዋል።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ መቀመጫውን በአሜሪካ ካደረገ የኢትዮ አሜሪካ የንግድ ምክር ቤት አባላት ጋር ተወያዩ።

ኢትዮጵያ ለቀጠናው ብቻ ሳይሆን ለዓለም አቀፍ ገበያም ኃይልን ለመላክ አቅዳለች ያሉት ክቡር ሚንስትር ዴኤታ  ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ የግሉን ዘርፍ በሀገሪቱ የሀይል ልማት መስክ ማሳተፍ ለጥራት፣ ለኃይል ማመንጫ እና ለኤክስፖርት እንዲሁም በተወዳዳሪ ዋጋ ኃይልን ለማቅረብ ያለውን አበርክቶ በአ

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ በውሃና ኢነርጂ ዘርፍ ከተሰማሩ የአረብ ኤምሬት ካምፓኒ ልዑካን ጋር ምክክር አደረጉ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ኢትዮጲያ በኢነርጂ ልማት ዘርፍ ምስራቅ አፍሪካን ተሻግሮ እስከ ደቡብ አፍሪካ ድረስ ከዚያም የሚያልፍ የተሳሰረ የኢነርጂ ተደራሽነትን ለማስፋት ራዕይ ሰንቃ እየሰራች መሆኑንም ገልጸዋል።

የኮዋሽ ምዕራፍ አምስት ቀጣይነት ብቻ ሳይሆን የዜጎቻችን ሕይወት ላይ ዘላቂ ለውጥ እንደሚያመጣ ተገለጸ፡፡

ክቡር  ዲኤታ አምባሳደር ደ/ር አስፋው ዲንጋሞ COWASH ለረጅም ጊዜ ማህበረሰብ-መር ልማት መለኪያ ሆኖ ማልገሉን ገልጸው ይህም የገጠር አካባቢ አገልግሎቶችን ለማስፋፋት ቁልፍ ተግባር መሆኑንና የኢትዮጵያን የውሃ፣ የንፅህና እና የንፅህና (WASH) መሠረተ ልማት ለማስቀጠል የሚያስፈልገውን የተቋማዊ

በቤዚን አቀፍ ዘላቂነት ማረጋገጫ (BaSRINET) ፕሮጀክት ለአዋሽ እና ለዋቢሸበሌ ቤዚን የተፋሰስ ዕቅድ ዝግጅት ስልጠና እየተሰጠ ነው።

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ የሚሰሩና ሊሰሩ የታሰቡ ስራዎችን ለመተግበር በዕቅድ መመራት ስለሚያስፈልግ በተፋሰስ ልማት ዕቅድ አዘገጃጀት ዙሪያ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተዘጋጅቷል ብለዋል።

ክቡር ሚኒስትሩ ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የመሰረተ ልማት ሚኒስቴር ልኡካን ጋር ተወያዩ፡፡

ክቡር ሚኒስቴሩ ከልኡካኑ ጋር በነበራቸው ቆይታ ኢትዮጵያ ለናይል ወንዝ 86% አበርክቶ እያደረገች ቢሆንም የተፋሰሱ ሀገራትን በመደመር መርህ ለጋራ ብልፅግና እና ጥቅም በጋራ መቆም ይጠበቅብናል እያለች ትገኛለች ብለዋል፡፡

ፕሮጀክቶች ውጤታማ እንዲሆኑ በጥናት ላይ የተመሠረተ የአቅም ግንባታ ማዕቀፍ እንደሚያስፈልግ ተገለፀ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የብሔራዊ የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር የአቅም ግንባታ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት የሚያስችልና መሠረት የሚሆን የፍላጎት መገምገሚያ እና ግብዓት መሠብሰቢያ /need assessment /የዘርፉን ሀላፊዎችንና ከፍተኛ ባለሙያዎችን ያሳተፈ ወርክሾፕ በፒራሚድ ሆቴል እየተካሄደ ነው።

ከሞላው ማዕዳችን ሳይሆን ካለችን ጥቂት ነገር ተጋርተን በዓሉን በጋራ እናሳልፋለን። ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ በተቋሙ ግቢ ውስጥ በተዘጋጀው የማዕድ ማጋራት መርሀግብር በቦሌ ክፍለከተማ፣ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 04 ለሚገኙ አቅመ ደካሞች እና ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሰራተኞች የተለያዩ የበዓል መዋያ ግብዓቶችን ድጋፍ አድርጓል፡፡

ቴክኖሎጂን መጠቀም አማራጭ ሳይሆን ተመራጭ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡

ስልጠናውን ያስጀመሩት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የብቃትና ሰው ሀብት አስተዳደር ተወካይ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሔለን አበራ ስልጠናው በዘመናዊ የአሰራር ስርዓት ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር በተቋሙ እየተሰራ ያለው የሪፎርም አካል በመሆኑ፤ በቀጣይ ወረቀት አልባ የአሰራር ስርዓትን ተግባራዊ በማድረግ ፈጣንና ቀልጣ

በተከዜ ቤዚን የፀባ-ዓይና ንዑስ ተፋሰስ የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደርን እውን ለማድረግ ማሳያ ነው ተባለ።

የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ዶ/ር ሚካኤል መሀሪ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለፁት በሚኒስቴር መስሪያቤቱ የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ የገፀምድርና የከርሰምድር የውሃ ሀብትን ለመጠበቅ፣ ለመንከባከብና ለማስተዳደር በርካታ ስራዎች እየተሰራ እንደሆነ ገልፀው፤ የከተሞች መስፋፋትን ተከትሎ የውሃ ሀብቱን በአግባቡ ፍትሃዊ

የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች በሚጠበቀው ልክ እየተከናወኑ መሆኑን ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ገለጹ።

እንደዘርፍ ተቀናጅተን በመናበብ ወደ ዝግጅት ምእራፍ ስራዎች መግባታችን ትልቅ አቅም በመፍጠር በጣም ጥሩ የሚባሉ ስራዎችን ለማከናወን አስችሎናል; እንደ ተቋም የዲጅታል መተግበሪያዎችን በመጠቀም ስራዎች እየተተገበሩ መሆኑንና ተጠሪ ተቋማትም በዚሁ ልክ መተግበር እንዳለባቸው አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የአዳማ ከተማ የፍሳሽ ማጠሪያ ፕሮጀክት የግንባታ ስራን በይፋ አስጀመሩ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ መቀሌ ላይ ያስጀመርነውን የፍሳሽ ማጣሪያ ፕሮጀክት አዳማ ላይ ለማስጀመር ከአለም ባንክ በተገኘ 1.9 ቢሊን ብር በሚሆን ወጭ ተገንብቶ በቀጣዮቹ 18 ወራት ይጠናቀቃል ብለዋል።

የዘርፉን ባለሙያዎችና ሀላፊዎች ቴክኒካል ክፍተቶችን በመሙላት በውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ውጤታማ ስራ ለመስራት የሚያስችል ስልጠና ነክ ወርክሾፕ እየተካሄደ ነው።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የባዜርኔት ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ሞላ ረዳ የአቅም ግንባታ ስልጠናው ከዚህ ቀደምም ይሰጥ እንደነበረ ገልፀው ስልጠናው ቴክኒካል ክፍተቶችን ለመሙላት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዱለው ተናግረዋል።

ሶስት አማካሪዎች ከአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ጋር የውል ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የማህበረሰቡን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት በአጠቃላይ በፕሮጀክቱ ከተያዙት 110 ፕሮግራሞች በ55ቱ ወረዳዎች ከሚገነቡት መካከል እስከአሁን ድረስ የ22 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ በመገባደድ ላይ የሚገኙ ሲሆን ከ82,000 የማህበረሰብ

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ጥበቃ ስራን በተሻለ ንቅናቄ ለመምራት የሚያስችል የትግበራ ስምምነት ተፈረመ።

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ የባዘርኔት ፕሮጀክት በመጀመሪያው ምእራፍ እየተገበረ ያለው የአቅም ግንባታና ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ በመሆኑ በክልሉ ያሉ አካላትን በፕሮጀክቱ አተገባበር ላይ ያላቸውን አቅም ማጠናከርና ማዘጋጀት በእጅጉ አስፈላጊ ነው ብለዋል።

ውሃ የጋራና ውድ ሀብት በመሆኑ መሰረተ ልማቱን በማዘመን ሴቶችንና ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከውሃና መሬት ሀብት ማዕከል /WLRC/ ጋር በጋራ በመቐለ የፀባ-ዓይና ንዑስ ተፋሰስ ላይ የሚተገበረው የብራት ፕሮጀክት በተሰራው የዳሰሳ ጥናት ዙሪያ በሚካሄደው የውይይት መድረክ ላይ ውሃ የጋራና ውድ ሀብት በመሆኑ መሰረተ ልማቱን በማዘመን ሴቶችንና ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባ ተገለ

የ2018ዓ.ም. የግድቤን በደጄ ፕሮጀክት ትግበራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር አስፈጻሚ አካላት የስልጠና መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡

የንጹህ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ ታምሩ ገደፋ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ በክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ አነሳሽነት የተጀመረ ሲሆን ውሃ አጠር በሆኑ አካባቢዎች የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎችን በተለያየ መንገድ የሚገኘውን ውሃ በማሰባሰብ እጥረት በተከሰተ ወቅት ጥቅም ላይ የሚያውሉ

የሶላር ሚኒግሪድ ስራዎችን በህብረት ስራ ኤጀንሲዎች ለማስተዳደር የሚያስችል ስልጠና እየሰጠ ነው።

የዩኤንዲፒ ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ይመስላል ተፈራ ስልጠናው በዋናነት የአፍሪካ ሚኒግሪድ ፕሮግራም UNDP ፕሮጀክት የሚተገብራቸው ሚኒ ግሪዶች በህብረት ስራ ሞዴል መሆኑን ገልጸው እነዚህ በኦሮሚያ እና በሶማሌ ክልሎች የሚገኙ ህብረት ስራዎችን በማደራጀት በሚኒግሪድ ዙሪያ ያላቸውን መረዳት ለመጨመር ስራውን ለማስተዳደ

በፍትሃዊነት ላይ የተመሰረ የውሃ ምደባ ሰርዓት ለመገንባት ለባለድርሻ አካላት የሚዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።

የሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማሙሻ ሀይሉ የአዋሽ ተፋሰስ ለመስኖ፣ ለኢንዱስትሪ፣ ለግብርና ልማት የተሻለ እና ከሌሎች ተፋሰሶች ቀድሞ ወደ ልማት የገባ በመሆኑ ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ውስጥ በመንግስት፣ በግል ባለሀብቶችና በማህበረሰቡ ተሳትፎ የመስኖ ልማት የበለጠ የተስፋፋበት ነበር ብለዋል።

በተከዜ ተፋሰስ የፀባ-ዓይና ንዑስ ተፋሰስ የዳሰሳ ጥናትና የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ዕቅድ የባለድርሻ አካላት የግምገማ ዓውደጥናት እየተካሄደ ነው።

የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ዶ/ር ሚካኤል መሀሪ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ የውሃ ሀብት ተጠቃሚ የማድረግ፣ የማዳረስና የማስፋት ስራዎች እየተሰራ ነው ብለዋል።

የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች በጥሩ ሁኔታ እየተከናወኑ መሆኑ ተገመገመ።

በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪና የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የአብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ የተነሱ ሀሳቦች ላይ በሚገባ ማየትና ምላሽ መስጠት እንደሚገባ ገልጸው አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ተናግረዋል

በኔፕ-አዴሌ ፕሮጀክት ትግበራ መመሪያ እና በአካባቢ ጥበቃ አስተዳደር ስርአት ዙሪ ግንዛቤ መፍጠር የተሻለ አፈጻጸምን እንሚያመጣ ተገለጸ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም ትግበራን ለማሳለጥ ፕሮጀክቱን ለሚተገብሩ እና ለባለድርሻ አካላት የተለያዩ ቴክኒካል እና የአቅም ግንባታን ስራዎችን በማከናወን የኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራሙን ትግበራ ለማሳለጥ አቅምን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።