Mar 2026

የ88 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች የግንባታና የቧንቧ ዝርጋታ የግዥ ሂደት ቅድመ ሁኔታ ላይ ከዘርፉ የግል ድርጅቶች ጋር ውይይት ተደረገ።

ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በውሃ ሀብት አስተዳደር፣በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍና በኢነርጂው ዘርፍ ባለፉት 5 ዓመታት ሰፊ ስራ ተሰርቶ ፣በሶስቱም ዘርፍ በርካታ ፕሮጀክቶች ተገንብተው ለአገልግሎት በማብቃት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በኢትዮጵያ የኬንያ አምባሳደርን በቢሯቸው አነጋገሩ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ አምባሳደሩ በጋራ ለመስራት ለውይይት በመምጣቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው፣ ኢትዮጵያ ከኬንያ ጋር ያላት ግንኙነት ታሪካዊ ብቻ ሳይሆን በደም የተሳሰረ ቤተሰባዊ ግንኙነት ያለው መሆኑን በአጵንኦት ገልጸዋል።

ጠንካራ ተቋማዊ አቅም ለመገንባት የሴቶችን እኩልነትና መብት መደገፍ ያስፈልጋል ተባለ፡፡

ጠንካራ ተቋማዊ አቅም ለመገንባት የሴቶችን እኩልነትና መብት መደገፍ ያስፈልጋል ሲሉ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሱልጣን ወሊ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ ጊዜ “Give to gain” በሃገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ “የሴቶች ድምጽ ለእኩልነት እና ለበለጸገች ኢትዮጵያ" በሚ

ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ፣ ጥናት፣ ዲዛይንና ኤሌክትሮ መካናኒክ እቃዎች አቅርቦት ውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የህብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ በተገባው የውል ስምምነት መሰረት በሚፈለገው የጥራት ደረጃና በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ፕሮጀክቱን በማጠናቀቅ የህብረተሰቡ የመጠጥ ውሃ ችግር እንዲፈታ አሳስበዋል።

የመንግስት አስተዳደርና አደረጃጀት ማሳለጥ አምድ ላይ ውይይት ተደረገ።

የመንግስት አስተዳደርና አደረጃጀት ማሳለጥ አምድ ላይ መዋቅር ለማዘጋጀት የሚያስችል የስራ ፍሰት፣ የሚኒስቴር መ/ቤቱና የ3ቱ ተጠሪ ተቋማት የመዋቅር አደረጃጀት፣ የበፊቱን ውጤት መነሻ በማድረግ የቴክኒካል፣ የብቃትና የባህሪ ብቃት የተካተተበት የስራ መዘርዝር (Job description) እና ከጀማሪ እስከ ከፍተኛ ባለ

ልኡካን ቡደኑ በኢትዮጵያ ባካሄዱት ጉብኝት በተመለከቱት ለውጥ በእጅጉ መደመማቸውን ገለጹ፡፡

የዛምቤዚ የውሃ ተፋሰስ ኮሚሽን (zamcom) ከፍተኛ ልኡካን ኢትዮጵያ ከውሃ ጥበቃና ከተፋሰስ አስተዳደር ጋር በተገናኘ በምታካሂዳቸው ተግባራት ዙሪያ ልምድ ለመቅሰም ባካሄዱት ጉብኝት በእጅጉ መደመማቸውን ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ ለዛምቤዚ የውሃ ተፋሰስ ኮሚሽን ልኡካን በአረንጓዴ አሻራ ያላትን የካበተ ልምድ በስፋት እያካፈለች ነው።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ለልኡካኑ አስቀድመው የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ ያላት የውሃ ድርሻ 86 በመቶ እንደሆነና ይህንን በጋራ ለመጠቀም እንዲቻል ታችኞቹን የተፋሰስ ሀገራት ከግምት በማስገባት እያስተዳደረች መሆኑን አስገንዝበዋል።

በተቋሙ ለ 3ኛ ጊዜ የተካሄደው የረመዳን ወር የማፍጠር መርሃ ግብር የእስልምና እምነት የሚያዛቸውን ትዕዛዛት በተግባር ያሳየ መልካም ተግባር ነው ተባለ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ፣በሚኒስቴር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ፣ ከተቋሙ የተለያዩ የስራ ክፍሎች ስራ አስፈፃሚዎች፣ የተቋሙ ሙስሊም ማህበረሰብ እህቶችና ወንድሞች እንዲሁም ሌሎች ባለሙያዎች ናቸው።

የከርሰ ምድር ውሃ መረጃን በአግባቡ ማስተዳደር በሚል አጀንዳ የከፍተኛ ባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡

የብራይት ፕሮጀክት ማናጀር ዶ/ር ማማሩ አያሌው በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ የተቀናጀ የውሃ ሃብት አስተዳደርን ለማስፈን በሚደረጉ ክንዋኔዎች በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በርካታ ስራ እየሰራ መሆኑን አውስተዋል፡፡በመሆኑም በእነዚህ ተፋሰሶች ዙሪያ የተቀናጀ የውሃ ሃብት አስተዳደር ተግባራትን

የገጠር የመጠጥ ውሃ አገልግሎት አቅርቦት ዘላቂ እና ምቹ እንዲሆን ለማድረግ አስቻይና ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።

የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ዋና ሃላፊ ሚስተር ቪክተር ቫዝቄዝ ለተሳታፊዎች በበይነ መረብ በዋናነት ትኩረት አድርገው ካስተላለፉት ሃሳብ ለመገንዘብ እንደተቻለው በፕሮጀክቱ የተገነቡ የመጠጥ ውሃ ግንባታዎችን በዘላቂነት አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ ህብረተሰቡ፣የግል ድርጅቶች፣መንግስትና ሌ

የአንድ ቋት ብሄራዊ ዋሽ ፕሮግራም የሁለተኛው ፌዝ የስድስት ወር የፕሮጀክት አፈጻጸም ጥሩ ውጤት ማስመዝገቡ ተገለጸ፡፡

ክቡር ዶክተር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ የአንድ ቋት ብሄራዊ ዋሽ ፕሮግራም የሁለተኛው ፌዝ ያለፈው የስድስት ወር ትልቅ ለውጥ ያመጣንበትና ሁሉም ፕሮጀክቶች ላይ ጠንካራ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ስራዎች ሁሉ ከ50 ፐርሰንት በላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያ በውሃ ሃብት ልማት በሰራችው ሰፊ ስራ በርካታ ለውጦች ተመዝግበዋል - ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት ኢትዮጵያ ከውሀ ጋር የተገናኙ ሠፊ አብዮታዊ ስራዎች በማከናወኗ በርካታ ለውጦች ተመዝገቧል፤ ሀገራችን ኢትዮጵያ የበርካታ የተፈጥሮ ሃብት ባለቤት ናት ከእነዚህ መካከል የከርሰ ምድር ውሃ ሃብት ትልቁ ጸጋ መሆኑን ጠቁመዋል።

የአቅም ግንባታ ስልጠናው በኢነርጂ ዘርፉ ሙያዊ እገዛ ለማድረግ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተሳታፊዎች ገለጹ።

በታዳሽ ኢነርጂ ተለዋዋጭ የትግበራ ዕቅድ ላይ ትኩረት አድርጎ በራማዳ ሆቴል ለአራት ቀናት የዘለቀው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በኢነርጂ ዘርፍ ለሚከናወኑ ተግባራት ሙያዊ እገዛ ለማድረግ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተሳታፊዎች ገለጹ።

ኢትየጵያ የኃይል ልማት ፍኖተ ካርታዋን (Ethiopia National Energy Compact) በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው ጉባኤ ላይ አቀረበች - የካቲት 26/2018 ዓ/ም

የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር የተከበሩ ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ በጉባኤው የከሰዓት በኋላ መድረክ ላይ የኢትዮጵያን የኃይል ልማት ፍኖተ ካርታ (Ethiopian National Energy Compact) አቅርበዋል፡፡

ድርቅን መቋቋም የሚችል ባለብዙ መንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት (CR wash) የስራ ነባራዊ ሁኔታ ግምገማ ተካሄደ፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ሲሆኑ ድርቅን መቋቋም የሚችል ባለብዙ መንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት (climate resilient project) የዋን ዋሽ(one Wash) አንድ ቋት ፕሮግራም አንዱ ዘርፍ ሲሆን 34 በመቶ ሽፋን ተሰጥቶት ወደስራ የተገባበት ፕሮጀክት መሆኑን አመልክተው ከሁለት ወራት በ

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ የአፍሪካ ልማት ባንክ ልኡክን በቢሯቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ የአፍሪካ ልማት ባንክ ሉኡካኑን ባነጋገሩበት ወቅት ሚኒስቴር መ/ቤቱ አጋር ድርጅቶች ጋር እየተሰሩ ባሉ ፕሮግራሞች እና ፕሮጀክቶች ላይ ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ለተቋሙ ሰራተኞች "ስነምግባራዊ ውሳኔና የጥቅም ግጭትን መከላከል እና ማስተዳደር" በሚል መሪ ሃሳብ ስልጠና ተሰጠ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን ትልልቅ ፕሮጀክቶችን የሚያስተዳድር በመሆኑ ከሰው ሀብት፣ ከፋይናንስና ከሎጀስቲክ አንፃር ስነምግባርን ተከትለን አገልግሎት መስጠት እንድንችል ስነምግባራዊ ውሳኔ እና የጥቅም ግጭት ምንነትን በአግባቡ ተረድተን እንዴት መከላከልና ማስተዳደር ይቻላል የሚለውን ግንዛ

ከ120 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ጥናት፣ዲዛይንና ግንባታ ክትትል ውል ስምምነት ተፈረመ።

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የህብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ በተገባው የውል ስምምነት መሰረት በሚፈለገው የጥራት ደረጃና በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ፕሮጀክቱን በማጠናቀቅ የህብረተሰቡ የመጠጥ ውሃ ችግር እንዲፈታ አሳስበዋል።

የብሔራዊ ዋን ዋሽ ፕሮግራም የሁለተኛው ምእራፍ የ6 ወራት አፈጻጸም እየተገመገመ ነው።

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የብሔራዊ ዋን ዋሽ ፕሮግራም የሁለተኛው ምእራፍ ማጠናቀቂያ ላይ እንደመሆናችን የተጀመሩትን ፕሮጀክቶች በውጤታማነት በመፈጸም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ትልቁ ትኩረት ሰጥተን የምንተገብረው ነው ብለዋል።

በኢነርጂ ልማት ዘርፍ በአግባቡ ያልተሰራ ዕቅድ ለሃይል እጥረት መከሰት ምክንያት ስለሚሆን ጥንቃቄ እንደሚሻ ተገለፀ።

ክቡር ዶ/ር ኢንጅነር ሱልጣን ወሊ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ ከመጣው የሃገሪቱ የህዝብ ብዛትና የኢኮኖሚ ፍላጎት ጋር በተገናኘ በቂ የሆነ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ በሚከናወኑ ተግባራት ጥራት ያለው ዕቅድ ሁነኛ ሚና ስለሚጫወት በዘርፉ ለሚሰሩ ተግባራት በጥንቃቄ አቅዶ መመራት ያስፈልጋልም ብለዋል።

የጎርፍ ክስተትን በመከላከል ከተጋላጭነት ይልቅ ለዘላቂ ልማት ማዋል ይገባል ተባለ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የውይይት መድረክ የማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ የጎርፍ ክስተትን በመከላከል ከተጋላጭነት ይልቅ ለዘላቂ ልማት ማዋል እንደሚገባ ገለፁ።

"በአድዋ ድል ሉአላዊነታችንን እንዳስከበርን የምግብ ሉአላዊነታችንን ለማረጋገጥም መረባረብ ይጠበቅብናል!"_ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ

በኢትዮጵያ ሉአላዊነት ጉዳይ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አርበኛ ነው ያሉት ክቡር ሚኒስትሩ የውሃ ሃብታችንና የኢነርጂ ልማታችን የሃገሪቱን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ሁነኛ ሚና ስለሚጫወት በዘርፉ ተግተን ልንሰራ ይገባናል ብለዋል።

በጣሪያ የፀሐይ ኃይል ልማት ብሔራዊ መመሪያ ላይ ውይይት ተደረገ።

የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ውይይቱ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውና ከፍተኛ ጠቀሜታ ባለው የጣሪያ የፀሐይ ኃይል ልማት እና አጠቃቀም ብሔራዊ ሰነድ ላይ ለመወያየት እና ለማጥራት ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች እና የኦሞ ጊቤ ቤዚን የጎርፍ ተጋላጭነት ቅነሳ የቅድመ ጥናት ሪፖርት ላይ ውይይት እየተካሄደ ነው።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከዚህ ቀደም የአዋሽ ቤዚን የጎርፍ ተጋላጭነት ቅነሳ ቅድመ ጥናት ሪፖርት ላይ ውይይት መደረጉን አስታውሰው፤ ጥናቱ የህብረተሰቡን የጎርፍ ተጋላጭነት ለመቀነስ በማን፣ ምንና መቼ ይተገበራል የሚለውንም የሚመልስና በሙያዊ ስነምግባር ሊተገበር የሚገባ መሆን እንዳለበት ጠቁመዋል።

ከ571 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚገነባው የአለታ ጩኮ ወረዳ የባለብዙ መንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት አፈፃፀሙ ከ80 በመቶ በላይ ነው ተባለ።

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከ80 ሺህ በላይ ህዝብ ተጠቃሚ ያደርጋል ያሉት የአለታ ጩኮ ከተማ ከንቲባ አቶ ቶርባ ቶሼ በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢዎችና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች የመስክ ምልከታ ላይ ተገኝተው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተ

ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ፣ ጥራትና በጀት ጀምሮ የመጨረስ አቅም የታየበት መሆኑን ቋሚ ኮሚቴው ገለፀ።

የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢዎችና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከለጋሽ ድርጅቶች ጋር በጋራ በሲዳማ ክልል ዙሪያ የተሰሩ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን ያሉበትን ደረጃ የመስክ ምልከታ ግብረመልስ በሰጡበት ወቅት ከክልሉ ጋር በጋራ የተሰሩት የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ፣ ጥራትና በጀ

"የከፍተኛ አመራሩ አርአያነት ለጸረ ሙስና ትግል" በሚል መሪ ቃል ለውሃና ኢነርጂ ዘርፍ አመራሮች ስልጠና ተሰጠ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የዛሬው የስልጠና መድረክ ዋና ዓላማ የስራ ሀላፊዎችና ሰራተኞች ለዜጎች አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት ከሀላፊነታቸው ጋር በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ መንገድ የጥቅም ግጭት ውስጥ ሊከታቸው የሚችሉ ሁኔታዎች ሲያጋጥሟቸው ግጭቱን መከላከል ወይንም በአግባቡ ማስተዳደር እንዲችሉና ሙስናን መከላከ

የአለታ ወንዶ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በቀጣይ ሁለት ወራት አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተባለ።

የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢዎችና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሲዳማ ክልል የአለታ ወንዶ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት አፈፃፀሙን በጎበኙበት ወቅት ፕሮጀክቱ በቀጣይ ከሁለት ወራት በኋላ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተብሏል።

ተፋሰስን ማልማት ለኢነርጂና ለመጠጥ ውሀ መሰረት በመሆኑ በአግባቡ ሊሰራበት ይገባል ፡፡ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ

በሚኒስቴር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስቴሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ ያለንን የገፀ ምድርና የከርሰ ምድር የውሃ መጠንና ጥራት በጥናት ማረጋገጥ ተገቢ መሆኑንና በዚህ ዙሪያም በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ቢሆንም የሚቀሩ ስራዎችም አሉ ብለዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በኢትዮጵያ የጣሊያን አምባሳደር ከተመራ ልዑክ ጋር ተወያዩ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ኢትዮጵያ ከለውጡ ወድህ በተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ተፋሰሶችን በማስተዳደር ፣ታለቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በርከታ ግድቦችን በመገንባትና በማጠናቀቅ በዘርፉ ውጤታማ መሆን እነደቻለች ገልጸዋል ።

የ2018 በጀት ዓመት የቤዚን አስተዳደር ጽህፈት ቤቶች የስድስት ወራት አፈጻጸም የግምገማ ሪፖርት ቀረበ፡፡

ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ የሚቀርበው ሪፖርት መነሻ በማድረግ በግማሽ ዓመቱ በአፈጻጸም ደረጃቸው የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀጠል፣በክፍተት የተለዩትን ደግሞ በቀሪ ስድስት ወራት ትኩረት ተሰጥቶባቸው የተቀናጀ የስራ መርሃ ግብር በማዘጋጀትና በመተግበር ዓመታዊ ግቡን ማሳካት ስለሚያስችል መድረኩ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል

ናይል ቀጣናዊ ትብብርን የማጠናከር ግዙፍ አቅም አለው – ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር)

ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት፥ ለናይል ተፋሰስ ዘላቂ ዋስትና የማህበረሰቡን በተለይም የወጣቶችን እና የሴቶችን አቅም በማጎልበት አሳታፊ እና ዘላቂ የውሃ ሀብት አስተዳደር ያስፈልጋል ብለዋል።

በኢትዮጵያ 98 የሶላር የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች እየተገነቡ መሆኑ ተገለጸ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች ከዋናው የሀይል መስመር ርቀው የሚገኙ አካባቢዎችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ 98 የሶላር የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን እያስገነባ መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም የአዴሌ (የብርሃን ተደራሽነት ለሁሉም) ፕሮጀክ

Feb 2026

የ24 ሰዓት የመብራት አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸው በርካታ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትሩፋቶችን እንዳስገኘላቸው ተጠቃሚዎች ተናገሩ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎችም በክልሉ ተገንብተው አገልግሎት መስጠት በጀመሩት የሶላር ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ዙሪያ ከተጠቃሚዎቹ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ የማህበረሰቡ ክፍሎች በከፍተኛ ሁኔታ መደስታቸውን አረጋግጠውላቸዋል።

ለፕሮጀክቶች ውጤታማነት የባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሰራርና የህብረተሰቡ ቁርጠኛ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።

በኢብሮ ሰዴን ተራራ ላይ የእርከን ቁፋሮ ስራ የተጀመረው የባዜርኔት /BaSRINET/ፕሮጀክት አስተባባሪ፣የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና የፕሮጀክቱ የዘርፉ ባለሙያዎች ፣ ከግብርና ሚኒስቴር በየደረጃው ያሉ የተፈጥሮ ሀብትና የመስኖ ባለሙያዎች፣ ስራውን በባለቤትነት የሚያስቀጥሉ የወረዳውና የቀበሌው ባለድርሻ አካላት ከማህበረሰ

ኢትዮጵያ ከፀሃይ ሃይል ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅሟን ለማሳደግ በርካታ ተግባራት እያከናወነች መሆኑ ተገለፀ።

በሃገሪቱ ከዋናው መስመር በከፍተኛ ርቀት ላይ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን ኤሌክትሪክ ሃይል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማገዝ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከዓለም ባንክ በተገኘ የብድር ድጋፍ በሚኒግሪድ መስመር ዝርጋታና በሶላር ሆም ሲስተም ለማዳረስ በስፋት እየተሰራ መሆኑን ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ 

1000ኪሎ ዋት ሀይል የሚያመነጨው የሶላር ሀይል ፕሮጀክት አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ የፕሮጀክቱን ስራ መጀመር አስመልክቶ በተዘጋጀው መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር የጋሻሞ የሶላር ሀይል ማመንጫ ከ400 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተገነባና ከ6ሺ በላይ አባውራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ብለዋል።

ክቡር ሚኒስትሩ የድሬዳዋ ከተማ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጠራቀሚያ፣ ማጣሪያና ማስወገጃ ፕሮጀክት ግንባታን አስጀመሩ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በድሬዳዋ ከተማ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጠራቀሚያ፣ ማጣሪያና ማስወገጃ የፕሮጀክት ግንባታን አስጀመሩ፡፡ በመርሀግብሩ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ከተሞቻችን እያደጉ ቢሆንም በከተማ ስታንዳርድ ልክ ማሟላት የሚገባቸውን የከተማ ጥራትና ውበት ሳያገኙ ቆይተው፤ ዜጎችን ለተለያዩ በሽ

በባዘርኔት /BaSRINET/ ፕሮጀክት የሚተገበር የኢብሮ ሰዴን ማህበረሰብ ንዑስ ተፋሰስ ልማት ማስጀመሪያ መርሃግብር ተካሄደ።

በማስጀመሪያ መርሃግብር ላይ የባቢሌ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ኑሪ መሃመድ የለውጡ መንግስት እንደ ሀገር ትልልቅ ፕሮጀክቶችን እያቀደ በመተግበር ውጤታማ ስራ መስራቱን ጠቅሰው የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ይህን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለውን ፕሮጀክ በወረዳችን እንድተገበር ዕድሉን ስለሰጠን በወረዳው ህዝብና በራሴ ስም አመሰግናለ

የአንድ ቋት ብሄራዊ ዋሽ ፕሮግራም የሁለተኛው ፌዝ የመስክ ሱፐርቪዥን በሁሉም ክልሎች እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡

የሱፐርቪዥን ስምሪት ቅድመ ዝግጅቱን አስመልክቶ በተካሄደ መድረክ የተገኙት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሚኒስትር ዲኤታ ማእረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ሞቱማ መቃሳ (ተወካይ) የአንድ ቋት ብሄራዊ ዋሽ ፕሮግራም የሁለተኛው ፌዝ የስራ የመስክ ግምገማ እንደሚሄድ ገልጸዋል፡፡

የከተሞችን ንፁህና ለእይታ ማራኪ ለማድረግ በትኩረት እንሰራለን፡፡ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በድሬዳዋ ከተማ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጠራቀሚያ፣ ማጣሪያና ማስወገጃ የኦፕሬሽንና ጥገና ፕሮጀክት ግንባታ የመሰረት ድንጋይ ባስቀመጡበት ወቅት ከተሞችን ንፁህና ለእይታ ማራኪ ለማድረግ በትኩረት እንሰራለን ብለዋል፡፡

የዓለም ባንክ ከአፍሪካ ህብረት የልማት ኤጀንሲ (AUDA–NEPAD) ጋር በመሆን በምስራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ሀገራት ለሚገኙ የውኃ እና ፋይናንስ ሚንስትሮች ጋር ተወያዩ።

የውሃና ኢነርጂ ሚንስቴር ሚንስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በመደረኩ ላይ ተገኝተው ኢትዮጵያ በቀጣይ ዓመታት በዘርፉ ልታከናውናቸው በያዘቻቸው ፕሮግራሞች ዙሪያ ጽሑፍ አቅርበዋል፡፡

የዲግ ከተማ የ24 ሰዓት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ሆነች።

የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ በዲግ ከተማ ተገኝተው እንደሚኒስቴር መስሪያ ቤት ከዋናው የሀይል መስመር ርቀው የሚገኙ አካባቢዎችን በሶላር ሀይል ተጠቃሚ ለማድረግ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ብለዋል።

ኢትዮጵያ የአረንጓዴ ኢነርጂ አቅሟን በስፋት ለማልማት ከግሉ ዘርፍ ጋር ለመስራት ከፍተኛ ፍላጎት አላትበኢነርጂ ዘርፍ ልማትና አቅርቦት ከተሰማራው KP Group ከተሰኘው የህንድ ኩባንያ ልዑካን ቡድን ጋር ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል፡፡

የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ በኢነርጂ ዘርፍ ልማትና አቅርቦት ከተሰማራው KP Group ከተሰኘው የህንድ ኩባንያ ልዑካን ቡድን ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡

የውኃ እና ኢነርጂ ሚንስቴር ሚንስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በዓለም ባንክ የዓለም አቀፍ ኦፕሬሽን ዋና ዳይሬክተር አና በጀርዴን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ሉኡካኑን ባነጋገሩበት ወቅት ሚኒስቴር መ/ቤቱ ከሌሎች የፌደራል ተቋማት እና አጋር ድርጅቶች ጋር እየተሰሩ ባሉ ፕሮግራሞች እና ፕሮጀክቶች ላይ ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡