Jan 2026

የደንበል ሀይቅን ከእንቦጭ አረም ለመታደግ የሁሉም ህብረተሰብ ሀላፊነት መሆኑ ተገለጸ።

"መጤ የእንቦጭ አረምን ከደንበል ሃይቅ ላይበጋራ እናስወግድ!! "በሚል መሪ ቃል የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ልማት ጽ/ቤት ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ባቱ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በጋራ በተዘጋጀው የህብረተሰብ ንቅናቄ ላይ የደንበል ሀይቅን መጠበቅ የሁሉም ህብረተሰብ ሀላፊነት መሆኑ ተገለጸ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮዎችና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት እቅድ አፈጻጸምን እየገመገመ ነው።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ አፈጻጸማችን በየጊዜው በተለያዩ የሀገራችን ከተሞች እየተዘዋወርን ስንገመግም ትልቅ የሆነን የውሃ ሀብት የምንመራና የምናስተዳድር እንደመሆናችን አንዳችን ከሌላችን ተሞክሮን በመውሰድ በዘርፉ የተሻለ ሰራ ለመስራት ስለሚያስችለን ነው ብለዋል።

በክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የተመራ ቡድን የነቀምቴ አካባቢ የልማት ስራዎችን ገበኙ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የተመራ ቡድን በነቀምቴ አካባቢ እየተገነባ ያለውን ዘመናዊ የፍሳሽ ማጣሪያ ፕሮጀክት ፣ 274 ሺ የከተማውንና አካባቢውን ማህበረሰብ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ እያደረገ ያለውን የጫንጮ ግድብ እና የውሃ ትሪትመንት ማእከል እየሰጠ ያለውን አገልግሎት ተመልክተዋል።

ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ በሐይደሮሎጂና ተፋሰስ መረጃ አስተዳደር መሪ ስራ አሰፈፃሚ እየተዘጋጁ ያሉ ሰነዶችን ገመገሙ፡፡

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስተሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞተማ መቃሳ በሐይደሮሎጂና ተፋሰስ መረጃ አስተዳደር መሪ ስራ አሰፈፃሚ እየተዘጋጁ ያሉ ሰነዶችን ገምግመዋል።

የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የስድስት ወራት እቅድ አፈጻጸም እየተገመገመ ነው።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ መደረኩ ላለፉት ስድስት ወራት በየዘርፉ የተከናወኑ በርካታ ጠንካራ ስራዎችን የምናስቀጥልበትና በቀጣይ ትኩረት አድርገን የምንተገብራቸውን በጋራ በመገምገም የበለጠ ውጤታማ እንድንሆን የምንችልበትን ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው ብለዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከ115 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የማማከር ውል ስምምነት ፈጸመ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ስምምነቱ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከሚያከናውናቸው ዘርፈ ብዙ ተግባራት አንዱ የሆነው የሳኒቴሽን መሠረተ ልማት ግንባታ በከተሞች አካባቢ የተሳለጠ አገልግሎት በሚሰጡበት ደረጃ ለማድረስ ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ችግር ፈቺ ሊሆኑ ይገባል ተባለ።

በቤዚን አቀፍ ዘላቂነት ማረጋገጫ ፕሮጀክት (BaSRINET) በአዋሽ ቤዚን ያንጉዲ ካችመንት፣ በዋቢሸበሌ ቤዚን ኦሮሚያ ክልል ባቢሌ ወረዳ ኢፋዴን ካችመንት እና በሶማሌ ክልል ዋቢ ሸበሌ ዞን አሎኢገርሲ ካችመንት ላይ ለሚተገበረው የተፋሰስ ዕቅድ ዝግጅት ዙሪያ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና የማጠቃለያ መርሃግብር ላይ የአቅም

የውሃ ጥናትና ዲዛይን እንዲሁም የፕሮጀክቶችን ቀጣይነትን ለማረጋገጥ ከሚደግፉ አማካሪ ድርጅቶች ጋር ውል ተፈረመ።

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የውሃ ጥናትና ዲዛይን ስራዎችን ከሚያከናውን እና የፕሮጀክቶችን ቀጣይነትን ለማረጋገጥ ከሚደግፉ አማካሪ ድርጅቶች ጋር የውል ስምምነት አድርገዋል።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ መቀመጫውን በአሜሪካ ካደረገ የኢትዮ አሜሪካ የንግድ ምክር ቤት አባላት ጋር ተወያዩ።

ኢትዮጵያ ለቀጠናው ብቻ ሳይሆን ለዓለም አቀፍ ገበያም ኃይልን ለመላክ አቅዳለች ያሉት ክቡር ሚንስትር ዴኤታ  ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ የግሉን ዘርፍ በሀገሪቱ የሀይል ልማት መስክ ማሳተፍ ለጥራት፣ ለኃይል ማመንጫ እና ለኤክስፖርት እንዲሁም በተወዳዳሪ ዋጋ ኃይልን ለማቅረብ ያለውን አበርክቶ በአ

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ በውሃና ኢነርጂ ዘርፍ ከተሰማሩ የአረብ ኤምሬት ካምፓኒ ልዑካን ጋር ምክክር አደረጉ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ኢትዮጲያ በኢነርጂ ልማት ዘርፍ ምስራቅ አፍሪካን ተሻግሮ እስከ ደቡብ አፍሪካ ድረስ ከዚያም የሚያልፍ የተሳሰረ የኢነርጂ ተደራሽነትን ለማስፋት ራዕይ ሰንቃ እየሰራች መሆኑንም ገልጸዋል።

የኮዋሽ ምዕራፍ አምስት ቀጣይነት ብቻ ሳይሆን የዜጎቻችን ሕይወት ላይ ዘላቂ ለውጥ እንደሚያመጣ ተገለጸ፡፡

ክቡር  ዲኤታ አምባሳደር ደ/ር አስፋው ዲንጋሞ COWASH ለረጅም ጊዜ ማህበረሰብ-መር ልማት መለኪያ ሆኖ ማልገሉን ገልጸው ይህም የገጠር አካባቢ አገልግሎቶችን ለማስፋፋት ቁልፍ ተግባር መሆኑንና የኢትዮጵያን የውሃ፣ የንፅህና እና የንፅህና (WASH) መሠረተ ልማት ለማስቀጠል የሚያስፈልገውን የተቋማዊ

በቤዚን አቀፍ ዘላቂነት ማረጋገጫ (BaSRINET) ፕሮጀክት ለአዋሽ እና ለዋቢሸበሌ ቤዚን የተፋሰስ ዕቅድ ዝግጅት ስልጠና እየተሰጠ ነው።

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ የሚሰሩና ሊሰሩ የታሰቡ ስራዎችን ለመተግበር በዕቅድ መመራት ስለሚያስፈልግ በተፋሰስ ልማት ዕቅድ አዘገጃጀት ዙሪያ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተዘጋጅቷል ብለዋል።

ክቡር ሚኒስትሩ ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የመሰረተ ልማት ሚኒስቴር ልኡካን ጋር ተወያዩ፡፡

ክቡር ሚኒስቴሩ ከልኡካኑ ጋር በነበራቸው ቆይታ ኢትዮጵያ ለናይል ወንዝ 86% አበርክቶ እያደረገች ቢሆንም የተፋሰሱ ሀገራትን በመደመር መርህ ለጋራ ብልፅግና እና ጥቅም በጋራ መቆም ይጠበቅብናል እያለች ትገኛለች ብለዋል፡፡

ፕሮጀክቶች ውጤታማ እንዲሆኑ በጥናት ላይ የተመሠረተ የአቅም ግንባታ ማዕቀፍ እንደሚያስፈልግ ተገለፀ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የብሔራዊ የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር የአቅም ግንባታ ማዕቀፍ ለማዘጋጀት የሚያስችልና መሠረት የሚሆን የፍላጎት መገምገሚያ እና ግብዓት መሠብሰቢያ /need assessment /የዘርፉን ሀላፊዎችንና ከፍተኛ ባለሙያዎችን ያሳተፈ ወርክሾፕ በፒራሚድ ሆቴል እየተካሄደ ነው።

ከሞላው ማዕዳችን ሳይሆን ካለችን ጥቂት ነገር ተጋርተን በዓሉን በጋራ እናሳልፋለን። ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ በተቋሙ ግቢ ውስጥ በተዘጋጀው የማዕድ ማጋራት መርሀግብር በቦሌ ክፍለከተማ፣ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 04 ለሚገኙ አቅመ ደካሞች እና ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ሰራተኞች የተለያዩ የበዓል መዋያ ግብዓቶችን ድጋፍ አድርጓል፡፡

ቴክኖሎጂን መጠቀም አማራጭ ሳይሆን ተመራጭ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡

ስልጠናውን ያስጀመሩት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የብቃትና ሰው ሀብት አስተዳደር ተወካይ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሔለን አበራ ስልጠናው በዘመናዊ የአሰራር ስርዓት ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥ እንዲኖር በተቋሙ እየተሰራ ያለው የሪፎርም አካል በመሆኑ፤ በቀጣይ ወረቀት አልባ የአሰራር ስርዓትን ተግባራዊ በማድረግ ፈጣንና ቀልጣ

በተከዜ ቤዚን የፀባ-ዓይና ንዑስ ተፋሰስ የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደርን እውን ለማድረግ ማሳያ ነው ተባለ።

የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ዶ/ር ሚካኤል መሀሪ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለፁት በሚኒስቴር መስሪያቤቱ የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ የገፀምድርና የከርሰምድር የውሃ ሀብትን ለመጠበቅ፣ ለመንከባከብና ለማስተዳደር በርካታ ስራዎች እየተሰራ እንደሆነ ገልፀው፤ የከተሞች መስፋፋትን ተከትሎ የውሃ ሀብቱን በአግባቡ ፍትሃዊ

የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች በሚጠበቀው ልክ እየተከናወኑ መሆኑን ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ገለጹ።

እንደዘርፍ ተቀናጅተን በመናበብ ወደ ዝግጅት ምእራፍ ስራዎች መግባታችን ትልቅ አቅም በመፍጠር በጣም ጥሩ የሚባሉ ስራዎችን ለማከናወን አስችሎናል; እንደ ተቋም የዲጅታል መተግበሪያዎችን በመጠቀም ስራዎች እየተተገበሩ መሆኑንና ተጠሪ ተቋማትም በዚሁ ልክ መተግበር እንዳለባቸው አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የአዳማ ከተማ የፍሳሽ ማጠሪያ ፕሮጀክት የግንባታ ስራን በይፋ አስጀመሩ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ መቀሌ ላይ ያስጀመርነውን የፍሳሽ ማጣሪያ ፕሮጀክት አዳማ ላይ ለማስጀመር ከአለም ባንክ በተገኘ 1.9 ቢሊን ብር በሚሆን ወጭ ተገንብቶ በቀጣዮቹ 18 ወራት ይጠናቀቃል ብለዋል።

የዘርፉን ባለሙያዎችና ሀላፊዎች ቴክኒካል ክፍተቶችን በመሙላት በውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ውጤታማ ስራ ለመስራት የሚያስችል ስልጠና ነክ ወርክሾፕ እየተካሄደ ነው።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የባዜርኔት ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ሞላ ረዳ የአቅም ግንባታ ስልጠናው ከዚህ ቀደምም ይሰጥ እንደነበረ ገልፀው ስልጠናው ቴክኒካል ክፍተቶችን ለመሙላት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዱለው ተናግረዋል።

ሶስት አማካሪዎች ከአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ጋር የውል ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የማህበረሰቡን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት በአጠቃላይ በፕሮጀክቱ ከተያዙት 110 ፕሮግራሞች በ55ቱ ወረዳዎች ከሚገነቡት መካከል እስከአሁን ድረስ የ22 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ግንባታ በመገባደድ ላይ የሚገኙ ሲሆን ከ82,000 የማህበረሰብ

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ጥበቃ ስራን በተሻለ ንቅናቄ ለመምራት የሚያስችል የትግበራ ስምምነት ተፈረመ።

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ የባዘርኔት ፕሮጀክት በመጀመሪያው ምእራፍ እየተገበረ ያለው የአቅም ግንባታና ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ በመሆኑ በክልሉ ያሉ አካላትን በፕሮጀክቱ አተገባበር ላይ ያላቸውን አቅም ማጠናከርና ማዘጋጀት በእጅጉ አስፈላጊ ነው ብለዋል።

ውሃ የጋራና ውድ ሀብት በመሆኑ መሰረተ ልማቱን በማዘመን ሴቶችንና ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከውሃና መሬት ሀብት ማዕከል /WLRC/ ጋር በጋራ በመቐለ የፀባ-ዓይና ንዑስ ተፋሰስ ላይ የሚተገበረው የብራት ፕሮጀክት በተሰራው የዳሰሳ ጥናት ዙሪያ በሚካሄደው የውይይት መድረክ ላይ ውሃ የጋራና ውድ ሀብት በመሆኑ መሰረተ ልማቱን በማዘመን ሴቶችንና ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባ ተገለ

የ2018ዓ.ም. የግድቤን በደጄ ፕሮጀክት ትግበራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር አስፈጻሚ አካላት የስልጠና መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡

የንጹህ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ስራ አስፈጻሚ አቶ ታምሩ ገደፋ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ በክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ አነሳሽነት የተጀመረ ሲሆን ውሃ አጠር በሆኑ አካባቢዎች የሚኖሩ የማህበረሰብ ክፍሎችን በተለያየ መንገድ የሚገኘውን ውሃ በማሰባሰብ እጥረት በተከሰተ ወቅት ጥቅም ላይ የሚያውሉ

የሶላር ሚኒግሪድ ስራዎችን በህብረት ስራ ኤጀንሲዎች ለማስተዳደር የሚያስችል ስልጠና እየሰጠ ነው።

የዩኤንዲፒ ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ይመስላል ተፈራ ስልጠናው በዋናነት የአፍሪካ ሚኒግሪድ ፕሮግራም UNDP ፕሮጀክት የሚተገብራቸው ሚኒ ግሪዶች በህብረት ስራ ሞዴል መሆኑን ገልጸው እነዚህ በኦሮሚያ እና በሶማሌ ክልሎች የሚገኙ ህብረት ስራዎችን በማደራጀት በሚኒግሪድ ዙሪያ ያላቸውን መረዳት ለመጨመር ስራውን ለማስተዳደ

በፍትሃዊነት ላይ የተመሰረ የውሃ ምደባ ሰርዓት ለመገንባት ለባለድርሻ አካላት የሚዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።

የሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማሙሻ ሀይሉ የአዋሽ ተፋሰስ ለመስኖ፣ ለኢንዱስትሪ፣ ለግብርና ልማት የተሻለ እና ከሌሎች ተፋሰሶች ቀድሞ ወደ ልማት የገባ በመሆኑ ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ውስጥ በመንግስት፣ በግል ባለሀብቶችና በማህበረሰቡ ተሳትፎ የመስኖ ልማት የበለጠ የተስፋፋበት ነበር ብለዋል።

በተከዜ ተፋሰስ የፀባ-ዓይና ንዑስ ተፋሰስ የዳሰሳ ጥናትና የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ዕቅድ የባለድርሻ አካላት የግምገማ ዓውደጥናት እየተካሄደ ነው።

የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ዶ/ር ሚካኤል መሀሪ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ የውሃ ሀብት ተጠቃሚ የማድረግ፣ የማዳረስና የማስፋት ስራዎች እየተሰራ ነው ብለዋል።

የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎች በጥሩ ሁኔታ እየተከናወኑ መሆኑ ተገመገመ።

በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪና የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የአብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ የተነሱ ሀሳቦች ላይ በሚገባ ማየትና ምላሽ መስጠት እንደሚገባ ገልጸው አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ተናግረዋል

በኔፕ-አዴሌ ፕሮጀክት ትግበራ መመሪያ እና በአካባቢ ጥበቃ አስተዳደር ስርአት ዙሪ ግንዛቤ መፍጠር የተሻለ አፈጻጸምን እንሚያመጣ ተገለጸ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም ትግበራን ለማሳለጥ ፕሮጀክቱን ለሚተገብሩ እና ለባለድርሻ አካላት የተለያዩ ቴክኒካል እና የአቅም ግንባታን ስራዎችን በማከናወን የኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራሙን ትግበራ ለማሳለጥ አቅምን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

Dec 2025

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደርን ተግባራዊ ለማድረግ የተመረጠው የወዴቻ ንዑስ ተፋሰስ በባለድርሻ አካላት ተጎበኘ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከውሃና መሬት ሀብት ማዕከል ጋር በጋራ በሚተገበረው የብሬይት ፕሮጀክት የወዴቻ ንዑስ ተፋሰስ ላይ የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደርን ተግባራዊ ለማድረግ የዳሰሳ ጥናት እና የ10 አመት እቅድ ተዘጋጅቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጎበታል።

በስድስት ከተሞች በሚገነባው ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያና ማስወገጃ ፕሮጀክት የትግበራ ሂደት ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት ምክክር ተካሄደ፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ መንግስት ትኩረት የተሰጠው ከተሞችን የማልማትና አረንጓዴና ፅዱ አካባቢን ከመፍጠር ተልዕኮ ጋር የተሳሰረ ቁርኝት ያለው በመሆኑ ከየቤቱ የሚወጣ ፍሳሽ ቆሻሻን በአግባቡ ለማስተዳደርና መልሶ ጥቅም ላይ ለማዋል የሚቻልበትን ሳይንሳዊ መንገድ በማመቻቸት የሚተገበር በመሆኑ ይህ

የዳሳሳ ጥናቱ ግኝትና ምክረ ሀሳብ መሬት ወርዶ ተግባራዊ ከሆነ የፕሮጀክቱ ዋና ተጠቃሚ እንደሚሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከውሃና መሬት ሀብት ማዕከል /Water and Land Resource Cente WLRC/ ጋር በመተባበር በብራይት /BRIGHT/ ፕሮጀክት አመቻችነትና አሳላጭነት በኢንፍራንዝ ንዑስ-ተፋሰስ የዳሰሳ ጥናትና የተፋሰስ ልማት ዕቅድ ላይ ለ3 ተከታታይ ቀናት ባህርዳር ከተማ ሲካሄድ የነበረ የባለድርሻ

ሰነዶቹ ለትግበራ በሚመችና በሀገራዊ የሪፎርም አቅጣጫ መሰረት በጥራት እየተዘጋጁ መሆኑ ተገለጸ።

በውሃና ኢነርጂ ዘርፍ የአገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍ ስራዎችን አስመልክቶ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ክፍል በቢሾፍቱ ሰራ አመራር ኢንስቲትዩት ተገኝቶ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የስትራቴጅክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚና የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ ሪፎርም የዋናው መስሪያ ቤት ቴክኒካል ኮሚቴ ሰብሳቢ እና የዝ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአማራ ክልል የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታን ከሚሰሩ ውሃቢሮ ፣ አማካሪ ድርጂቶችና ኮንትራክተሮች ጋር ተወያዬ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአማራ ክልል በመንግስት በጀት በሚደገፉ የCR-WaSH የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችሉ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን በተመለከተ ከክልል ውሃቢሮ ፣ አማካሪ ድርጂቶችና ኮንትራክተሮች ጋር ውይይት ያደረጉት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደ

በአዋሽ ተፋሰስ የወዴቻ ንኡስ ተፋሰስ የዳሰሳ ጥናትና የተፋሰስ አስተዳደር እቅድ ላይ ውይይት እየተደረገ ነው።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከውሃና መሬት ሀብት ማዕከል ጋር በጋራ የሚተገበረውና የብራት ፕሮጀክት አካል በሆነው በአዋሽ ተፋሰስ የወዴቻ ንኡስ ተፋሰስን ለማልማት በተካሄደው የዳሰሳ ጥናትና የአስተዳደር እቅድ ላይ ውይይት እየተደረገ ነው።

የኢንፍራንዝ ንዑስ-ተፋሰስ የዳሰሳ ጥናት እና የተቀናጀ የተፋሰስ ዕቅድ ዓውደ-ጥናት እየተካሄደ ነው።

ዶ/ር ሚካኤል መሀሪ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በአሁኑ ወቅት በውሃ አስተዳደር ዘርፍ፣ በኢነርጂ ዘርፍና በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሰፊ ስራ በመስራት ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበና ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን አንስተው የዕለቱ ዓውደ-ጥናት ቀጣይ በተፋሰሶች ላይ በተለይ በኢንፍራንዝ ንዑስ ተፋሰስ ላይና መሬት

በባዘርኔት ፕሮጀክት በአዋሽ ተፋሰስ ሊሰሩ በተመረጡ ሳይቶች ዙሪያ ጉብኝት መካሄዱ በቀጣይ ተግባራት ትልቅ ግብዓት ይሆናል-አቶ ሞላ ረዳ የባዘርኔት ፕሮጀክት አስተባባሪ

ከጉብኝቱ አንድ ቀን ቀደም ብሎ በአዋሽ ተፋሰስ ነባራዊ ሁኔታ የግምገማ ሪፖርት ማረጋገጫ አውደ ጥናት ቀርቦ በባለድርሻ አካላት ውይይት የተደረገበት መሆኑን አስታውሰው ይህንን ውይይት ተከትሎም የተመረጡ ሳይቶች ጉብኝት እንዲካሄድ መደረጉን አስታውሰው የተመረጡ ሳይቶች ለተቀናጀ ውሃ ሃብት አስተዳደር ምቹ መሆናቸውን ለመ

በባዘርኔት ፕሮጀክት የሚተገበረው የአዋሽ ተፋሰስ የነባራዊ ሁኔታ የግምገማ ሪፖርት ማረጋገጫ አውደ ጥናት ውይይት እየተካሄደ ነው።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በባዘርኔት ፕሮጀክት የሚተገበረው የአዋሽ ተፋሰስ ነባራዊ ሁኔታ የግምገማ ሪፖርት ማረጋገጫ አውደ ጥናት የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ በያንጉዲ ሆቴል እየተካሄደ ነው።

ወንድማማችነታችንን ለማጠናከር በውሃና ኢነርጂው ዘርፍ በጋራ እንሰራለን።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ለደቡብ ሱዳን የውሃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስቴር ለመጡ ልዑካን የተዘጋጀው የልምድ ልውውጥ እና የአቅም ግንባታ ስልጠና ማጠቃለያ መርሀ ግብር ላይ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ባደረጉት ንግግር ወንድማማችነታችንን ለማጠናከር በውሃና ኢነርጂው ዘርፍ በጋራ እ

የዩኤን ዲፒ (UNDP)ስቲሪንግ ኮሚቴ በፕሮጀክቱ እስካሁን በተሰሩ ስራዎችና በወደፊት አቅጣጫ ላይ ውይይት አደረገ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የዩኤንዲፒ/UNDP/አፍሪካ ሚኒግሪድ ፕሮግራም እስቲሪንግ/String/ኮሚቴ በፕሮጀክቱ እስካሁን በተሰሩ ስራዎች፣ በተዘረጉ አስቻይ ሁኔታዎች፣ በመጡ ለውጦችና በወደፊት አቅጣጫ ላይ ውይይአድርጓል።

በጣም ገጠራማ ለሆኑ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ሀይል ከሚያቀርቡ በዘርፍ ከተሰማሩ የ16 የግል ድርጅቶች ውል የማደስና ከ13 ተጨማሪ የግል ድርጅቶች ጋር ውል የመግባት ስነስርዓት ተካሄደ ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ኢትዮጵያ እምቅ የኢነርጂ ሀብት ያላት ሀገር እንደሆነና ከለውጡ ወዲህ እንደሀገር በዘርፉ ከፍተኛ ስራ ተሰርቶ ውጤት ምጣቱን ገልፀው ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ሙሉ በሙሉ ተደራሽ ለማድረግ ከፍተኛ ርብርብና ቅንጅታዊ አሰራርን ይጠይቃል ብለዋል።

ከ5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ የተገነባው የንጹህ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ።

አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ውሃ ላይ ያሉ ትልቁ ስኬታችን ጉድጓድ ተቆፍሮ ውሃ ሲወጣ እና ፕሮጀክቱ ህይወት ዘርቶ ወደ ህብረተሰቡ ሲደርስ ነው በማለት የወረዳው ነዋሪዎች የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ በመሆናቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል።

በዘርፉ የተመዘገበውን ለውጥ ለማስቀጠል ከአጋር አካላት ጋር በጋራ መስራት የጎላ ሚና አለው።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር Mr. Sune Krogstrup ጋር በከርሰምድር ውሃ ካርታ (ground water mapping) እና በአቅም ግንባታው ዘርፍ በትብብር ለመስራት በሚያስችል ጉዳዮች ላይ ተወያዩ።

ለፕሮጀክቶች ውጤታማነት የአመራር ቁርጠኝነት ወሳኝ ነው ተባለ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በውሃ ሀብት አስተዳደር ከሚተገበሩ ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነው የባዘርኔት ፕሮጀክት በሶማሌ ክልል የቀላፎ ወረዳ አሎ አጋርሲ ተፋሰስ በተጎበኘበት ወቅት ለፕሮጀክቶች ውጤታማነት የአመራር ቁርጠኝነት ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ።

የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ከውሀ ሀብት እና ከመስኖ ልማት ሚኒስቴር የመጡ ልኡካን በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እየተተገበሩ ያሉ ስራዎችን ጎበኙ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ የውሀ ሀብት እና የመስኖ ልማት ሚኒስቴር የመጡ ልኡካንን የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ ተቋም የሆነውን የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንሰቲትዩት ፣የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት የአቃቂ ፍሳሽ ማጣሪያ ማእከልንና የአዳማ ከተማ ውሃ አገልግሎትን ጎብኘተዋል።

የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከስምንት አማካሪዎች ጋር የውል ስምምነት ተፈራረመ

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የማህበረሰቡን የመጠጥ ውሃ ተደራሽነት ለማስፋት በሚደረገው ጥረት እንደአጠቃላይ በፕሮጀክቱ ከተያዙት 110 ፕሮግራሞች ውስጥ በ55 ወረዳዎች በሚተገበሩ የንጹህ መጠጥ ውሃ ግንባታ ስራዎች የአቅም ግንባታና ከግንባታ በኋላ የፕሮጀክቶችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ እንዲያስችል ከአ

ለ22 ፕሮጀክቶች 26 እስታንድባይ ጀኔሬተሮች /standbygenerators/ የግዥ የውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰምድር ውሃ ፕሮጀክት የሚገነቡ በአጠቃላይ በ55 ወረዳዎች 110 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች እንዳሉ ገልፀው ጀኔሬተሮቹ የሚገዛላቸው 22ቱ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው ተጠናቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙና በመጠናቀቅ ላይ የሉ ናቸው ብለዋል።

ሀገራችን ያላትን የውሃ ሀብት እንድናውቅ የሚደረገው ጥረት በትምህርት ሊደገፍ ይገባል ሲሉ ተማሪዎች ገለጹ፡፡

የቪዥን አካዳሚ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ዲጂታል ኤግዚቢሽኑን በጎበኙበት ወቅት ሀገራችን ያላትን የውሃ ሀብት እንድናውቅ የሚደረገው ጥረት በትምህርት ሊደገፍ ይገባል ሲሉ ተማሪዎች ገለጹ፡፡

በሃዋሳ ከተማ ለሚገነባው ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያና ማስወገጃ ፕሮጀክት (Faecal Sludge and Septage Treatmenet Plant ) ግንባታና ጥገና የውል ስምምነት ተፈረመ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከአለም ባንክ በተገኘ የብድር ድጋፍ በ23 ከተሞች የሚተገበር የሁለተኛው የከተሞች መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት አካል የሆነው በሃዋሳ ከተማ የሚገነባው ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ እና ማስወገጃ ፕሮጀክት የኢትዮጵያ መንግስት ከተሞችን ጽዱ፣ ማራኪ እና ውብ ለማድረግ እያከናወነ ያለ