Jul 2026

ለኤረር CR-WASH ፕሮጀክት 48.7 ሚሊዮን ብር የአዋጭነት ጥናት፣ ዝርዝር ዲዛይንና የተግባር ስልጠና ውል ተፈረመ፡፡

በሱማሌ ክልል ለሚተገበረው የኤረር የአየር ንብረትን የሚቋቋም (Climate Resilient) የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን (CR-WASH) ፕሮጀክት ለማሳካት የሚያግዝ 48.7 ሚሊዮን ብር የአማካሪ አገልግሎት ውል በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መካከል ተፈርሟል።

የሀዋሳ ሀይቅን ደህንነት ለመጠበቅ የጋራ የባለድርሻ አካላት የስትሪንግ ኮሚቴ ውይይት እየተካሄደ ነው።

ሀይቁ ካለው ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ መስተጋብር አንጻር ሁሉም ባለድርሻ አካላት በጋራና በተናበበ መንገድ ለሀይቁ ዘላቂ ጠቀሜታ መስራት እንደሚገባ የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ቤዚን አስተዳደር ጽ/ቤት ሀላፊ/ተወካይ ዶ/ር ወንድሙ ታዲዎስ እንግዶችን እንኳን ደህና መጣቹ ባሉበት ወቅት ገልጸዋል።

በ319,728,520.00 ብር የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ለማልማትና ስራ ላይ ለማዋል የሚያስችል የውል ስምምነት ተፈረመ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በጋምቤላ እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች በ319,728,520.00 (ሦስት መቶ አስራ ዘጠኝ ሚሊዮን ሰባት መቶ ሃያ ስምንት ሺህ አምስት መቶ ሃያ ብር) የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ለማልማትና ስራ ላይ ለማዋል ከሁለት ኮንትራክተሮች ጋር ውል ተፈራረመ።

22ኛው የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር የሚኒስትሮች ምክር ቤት ጉባኤ ተጠናቀቀ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጅነር ሀብታሙ ኢተፋ በጉባኤው መጠናቀቂያ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ፣ ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር (EAPP) የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሊቀመንበርነትን ከግብፅ በይፋ መረከቧን ገልጸዋል።

በ312.2 ሚሊዮን ብር የጉራድሃሞሌ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የቧንቧና መገጣጠሚያ አቅርቦት ውል ተፈረመ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ፣ ፕሮጀክቱ በአካባቢው የመጠጥ ውሃ አቅርቦትን በማሻሻል የሕብረተሰቡን የኑሮ ደረጃ ከፍ ከማድረጉም ባሻገር፣ የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም የውሃ አቅርቦት ሥርዓት በመገንባት ዘላቂ ልማትን እንደሚያግዝ ገል

በአርባ ምንጭ ኩልፎ ወንዝ የሚከናወነው የአስቸኳይ ጊዜ የወንዝ ደለል ማስወገጃ ሥራ በተፋጠነ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ አቅጣጫ ተሰጠ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ የተመራ ቡድን፣ የኢትዮጵያ ጎርፍ መከላከል ፕሮጀክት አስተባባሪና የአርባ ምንጭ ከተማ ከፍተኛ አመራሮች በአርባ ምንጭ ከተማ በኩልፎ ወንዝ እየተከናወነ ያለውን የአስቸኳይ ጊዜ የወንዝ ደለል ክምችት ማስወገጃ ሥራ የመስክ ምል

የምስራቅ አፍሪካ የቀጠናዊ የኃይል ትስስር የአባል ሀገራቱን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የሚያጠናክር ነው! (ዶ/ር ኢንጂነር ሡልጣን ወሊ)

የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ኢንጂነር ሡልጣን ወሊ በመርሐ ግብሩ ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት የምስራቅ አፍሪካ የቀጠናዊ የኃይል ትስስር የአባል ሀገራትን የኤሌክትሪክ ሀይል ትስስር ከማጠናከር ባለፈ የዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውንም በእጅጉ ያጠናክራል ሲሉ ተናግረዋል።

የምስራቅ አፍሪካ የሀይል ትስስር 22ኛው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ በይፋ ተጀምሯል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚንስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ትስስር (Eastern Africa Power Pool) የተመሰረተው ሰፊ ዓላማን አንግቦ ሲሆን የቀጣናውና የጎረቤት ሀገራት ትብብር ስኬታማ የሚሆነው ሀገራት በፈቃዳቸው በጋራ ህጎች በመመራት ሲስማሙ ነው በሚለው መርህ መመራት ሲ

የጎርፍ ቀድሞ ማስጠንቀቂያ ሥርዓትን ለማጠናከር ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተካሄደ።

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አብደላ ከማል ሲሆኑ፣ በመክፈቻ ንግግራቸው ዩኒቨርሲቲው በውሃ ዘርፍ በርካታ ምርምሮችንና የማህበረሰብ አገልግሎቶችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸው፣ በተለይም ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር በውሃ ሀብት አስተዳደርና በጎርፍ አደጋ ቅነሳ ላይ ያለው ትብብር ወደፊትም በበለጠ ሊጠናከር

ኢትዮጵያ በEAPP ስብሰባ የቀጠናዊ የኤሌክትሪክ ገበያ (Day-Ahead Market) በአስቸኳይ እንዲጀመር ጥሪ አቀረበች፡፡

መንግሥት የቀጠናዊ የኤሌክትሪክ ገበያው መዘግየት አባል ሀገራት ከድንበር ተሻጋሪ የኤሌክትሪክ ንግድ የሚገኙ ኢኮኖሚያዊና ልማታዊ ጥቅሞችን እንዳይጠቀሙ እያደረገ መሆኑን ገልጾ፣ ተጨማሪ መዘግየት የቀጠናውን የኃይል ትስስር ግቦች እንደሚያስተጓጉል በመግለጽ፣ ገበያው በአስቸኳይ ወደ ሥራ እንዲገባ ጥሪ አቅርቧል።

በ6ኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዷል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በኢትዮጵያ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶችን በመገንባት የህዝብ ጥያቄን ለመፍታት እና የሀገሪቱን ብልፅግና ለማረጋገጥ የሚሰራው ስራ የሚደነቅ ነው፤ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁም ለኢትዮጵያ ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑንም ከቀረቡ አስተያየቶች መካከል

በአዋሽ ተፋሰስ ለሚገኙ ሴቶች በንግድና ሥራ ፈጠራ ላይ ያተኮረ ሥልጠና እየተሰጠ ነው።

በውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሴቶችና ማኅበራዊ አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ ወይዘሮ የውብዳር አሚኖ በሀገሪቱ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዲሁም ያላቸውን ሀብትና ንብረት እንዴት ማስተዳደር እንዳለባቸው ለማስገንዘብ በርካታ ሥራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ገልጸዋል።

በ6.2 ቢሊየን ብር ወጪ የተገነባው የአዳማ ከተማ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በይፋ ተመረቀ።

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ማኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ፕሮጀክቱ ከንድፍ ዝግጅት ጀምሮ እስከ ፍጻሜው ድረስ በርካታ የምህንድስና፣ የፋይናንስ፣ የአስተዳደርና የዓለም አቀፍ ፈተናዎችን በማለፍ የተጠናቀቀ ሀገራዊ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያን የሚመጥን የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ለማምጣት ታሳቢ ያደረገ የምዘና ስርዓት ያስፈልጋል። ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ

ክቡር ሚኒስትሩ በውይይቱ ወቅት በተቋም አገልግሎት ለማግኘትና ጉዳይ ለማስፈፀም ተገቢ ያልሆነና መጉላላትን በመቀነስ የዜጎችን የመገልገል መብት ለማክበር ሪፎር ወሳኝ ነው ብለዋል። ሰውም ሆነ ተቋም የሚቀረፀው በሚሰራው ስራ ልክ ነው ያሉት ክቡር ሚኒስትሩ ካልንበት የአሰራር ስርዓት በመሻገር የዜጎችን የመገልገል መብት

የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች የተፋሰሱን ስነ ምህዳር በመጠበቅ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ያግዛል ተባለ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በቤዚን አቅፍ የዘላቂነት ማረጋገጫ ፕሮጀክት /BaSRINET/ በኦሮሚያ ክልል ከምስራቅ ሀረርጌ ዞን ባቢሌ ወረዳ ኢብሮ ሳዴን ቀበሌ ለተውጣጡ ሴቶች የሚሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች የተፋሰሱን ስነ ምህዳር በመጠበቅ የሴትችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ያግዛል ተባለ።

የአረንጓዴ ዐሻራ ትሩፋት …

ዓለማችንን በአሁኑ ወቅት እየፈተኑ ከሚገኙ ጉዳዮች መካከል የአየር ንብረት ለውጥ ያስከተላቸው ጫናዎች በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ። ኢትዮጵያ ውሃን ጨምሮ ለተፈጥሮ ሃብት የአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነት ምላሽ ለመስጠት ተግባራዊ ርምጃ በመውሰድ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች።

የባዘርኔት ፕሮጀክት በዋቢ-ሸበሌ ተፋሰስ የህዝብ ንቅናቄን በመፍጠር የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎችን በስኬት እያከናወነ ነው።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የባዘርኔት (BaSERINET) የዋቢ-ሸበሌ ተፋሰስ ፕሮጀክት ከአቅም ግንባታ እና ስልጠናዎች ጎን ለጎን፣ በኢብሮ-ሰዴን ንዑስ ተፋሰስ (catchment) ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር እያከናወነ ያለው የአፈርና የውሃ ጥበቃ ሥራ ከፍተኛ ስኬት እያስመዘገበ መሆኑ ተገለጸ።

በታችኘው አዋሽ አፈርን በመጠበቅ ብልጽግናችንን እናረጋግጣለን በሚል መሪ ቃል የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ተጀመረ።

"አፈርን በመጠበቅ ብልጽግናችንን እናረጋግጣለን" በሚል መሪ ቃል በአዋሽ ተፋሰስ በያንጉዲ ከችመንት በባዘርኔት (Basernet) ፕሮጀክት የተጀመረው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ በይፋ ተጀምሮ በተሳካ ሁኔታ በመከናወን ላይ ይገኛል።

በቤዚን አቀፍ የዘላቂነት ማረጋገጫ ፕሮጀክት በማይክሮሶፍት ዘመናዊ የአሰራር ስርዓት በመታገዝ የሚገነባው አቅም ለተቀናጀ የውሃ ሃብት አስተዳደር ውጤታማነት!

በውሃና ኢነርጅ ሚኒስቴር የሚተገበረው የቤዚን አቀፍ የዘላቂነት ማረጋገጫ ፕሮጀክት (BaSRINET) በማይክሮሶፍት የተቃኘ ዘመናዊ አሰራርን በዘርፉ ለመተግበርና ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና በአዳማ ከተማ ሂል ሳይድ ሆቴል አዘጋጅቷል።

በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ለሚገነቡ 14 የውሃ ጉድጓዶች ቁፋሮ ከ370 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የስራ ውል ስምምነቶችን ተፈራረመ።

ስምምነቱን የተፈራረሙት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የህብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ በተገባው የውል ስምምነት መሰረት በሚፈለገው የጥራት ደረጃና በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ፕሮጀክቱን በማጠናቀቅ የህብረተሰቡ የመጠጥ ውሃ ችግር እ

የብሔራዊ ዋን ዋሽ ፕሮግራም የስቲሪንግ ኮሚቴ የ2018 ዓ.ም. አፈጻጸምን በመገምገም የ2019 ዓ.ም. ዕቅድን አጸደቀ።

የብሔራዊ ዋን ዋሽ (One WASH National Program–OWNP) የስቲሪንግ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባውን በራዲሰን ብሉ ሆቴል በማካሄድ የ2018 ዓ.ም. አጠቃላይ የፕሮግራሙን አፈጻጸም በመገምገም የ2019 ዓ.ም ዕቅድን አጽድቋል።

በባዘርኔት ፕሮጀክት የዋቢሸበሌ ቤዚንን ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የውሃ ሀብት አስተዳደርን ተግባራዊ ለማድረግ ከሚያግዙ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ የሆነው የባዘርኔት ፕሮጀክት/Basin Scale Resilience Initiative for Ethiopia/ የዋቢሸበሌ ቤዚንን ውጤታማ ለማድረግ በንግድና በስራ ፈጠራ ላይ ለተሰማሩ ሴቶች የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተ

በቀጣዮቹ አራት ዓመታት 100 በመቶ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትን ለማሳካት አዲስ የውሃና ሳኒቴሽን አስተዳደር ሞዴል ለውይይት ቀረበ።

መንግሥት በቀጣዮቹ አራት ዓመታት 100 በመቶ የኢትዮጵያን ህዝብ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽ ለማድረግ አቅዶ እየሰራ መሆኑን የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ።

የኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በመጠጥ ውኃ ጥራትና በአደጋ ስጋት ቅነሳ ዘርፍ ትብብር ሊጠናከር ነው።

የተከበሩ ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ፣ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የብሔራዊ አስቸኳይ ጊዜ፣ አደጋና ቀውስ አስተዳደር ባለሥልጣን (NCEMA) ሰብሳቢ የሆኑትን የተከበሩ አሊ ሳኢድ አል ነያዲን (H.E. Ali Saeed Al Neyadi) በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው በሁለትዮሽ ትብብር ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።

Jun 2026

የኢትዮጵያ የከርሰ ምድር ውሃ ጥናት እና የውሃ ጉዶጓድ ቁፋሮና ግንባታ መመሪያዎች ለባለድርሻ አካላት ቀርበው ግምገማ ተካሄደባቸው።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ አስቀድመው በከርሰ ምድር የውሃ ሃብት ዘርፍ በስራ ላይ የቆዩ፣ሲሰሩ የነበሩና አሁንም ስራውን በመምራት ላይ የሚገኙት ሙያተኞች እስከአሁን ላበረከቱት አስተዋፅኦ አመስግነው ይህ ተግባርም አበረታች ውጤት እያስመዘገበ ያለ በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በአጽንኦት አሳስበዋል።

ብሔራዊ የኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም (NEP 3.0) ፍኖተ ካርታ ላይ ውይይት ተካሄደ።

የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም (NEP 3.0) እ.ኤ.አ በ2035 ሁለንተናዊ አስተማማኝ፣ ተመጣጣኝ እና ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ለማስፈን የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ግብ ነው ብለዋል።

የብቃት ምዘናው የሪፎርሙን ስኬት የሚያረጋግጥ ወሳኝ መሳሪያ ነው። ዶ/ር ኢንጅነር ሀብታሙ ኢተፋ

በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢንጅነር ሀብታሙ ኢተፋ፣ የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ ሰራተኞች ጠንካሮችና ብቁ በመሆናቸው የብቃት ምዘናውን በውጤታማነት እንደሚያጠናቅቁ ያላቸውን እምነት በመግለጽ ሰራተኞቹን አበረታተዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ እየተሰራ ነው - ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ እየተሰራ መሆኑን በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ።

ውሃ ለሀይድሮ ፓወር፣ ለመስኖና ለመጠጥ ብቻ ሳይሆን ለሴቶችና ለልጃገረዶች በወር አበባቸው ወቅት ንፅህናቸውን በአግባቡ ለመጠበቅ የማይተካ ሚና አለው ተባለ።

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ረዳት አቶ ተስፋዬ ፊቻላ ሴቶችና ልጃገረዶች የወር አበባ ንፅህና መጠበቂያ ማግኘት ከፍተኛ ተግዳሮት የሆነባቸው በርካታ ሴቶች በገጠርም ሆነ በከተማ የሚገኙ ሲሆን የወር አበባቸውን ምቹ በሆነ ሁኔታ ማስተናገድ ካለመቻል የተነሳ ሴት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ቀሪ ማብዛት

በHuman Capital Project (HCP) አዘጋጅነት የባለድርሻ አካላት የአቅም ግንባታ ስልጠና መድረክ ተካሄደ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የHuman Capital Operation ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ ዱጉማ በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ በቁጥር መቶ በሚደርሱ የዓለም ሃገራት የሚተገበር መሆኑን አስረድተዋል።

በግንባታ ላይ የሚገኙ የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የቅርብ ክትትል እየተደረገ ነው - ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ፣ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃ፣ መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳዊት ሀይሉ ጨምሮ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ በዓለም ባንክ ድጋፍ እየተገነባ የሚገኘውን የንፁህ የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክትን

የተለያዩ ተቋማት ለሚሰጧቸው ልዩ ልዩ አገልግሎቶች የሚከፈሉ የአገልግሎት ክፍያዎችን ለመወሰን የቀረበው ረቂቅ ደንብ ወደ ስራ እንዲገባ ተወሰነ

ምክር ቤቱ ተወያይቶ ውሳኔ ካሳለፈባቸው 5 ጉዳዮች መካከል የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ተቋማት ለሚሰጧቸው ልዩ ልዩ አገልግሎቶች የሚከፈሉ የአገልግሎት ክፍያዎችን ለመወሰን የቀረበው ረቂቅ ደንብ ይገኝበታል።

በኢትዮጵያ የውሃ ዋጋ ትመና እና ዘላቂ አካታች እድገት ላይ ያተኮረ የውይይት ተካሄደ።

በሚኒስትር ዲኤታ ማእረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ እንደገለጹት የውሃ ሃብት የሀገሪቱ ኢኮኖሚ መሰረት፣ የምግብ ዋስትና ምሰሶ እና የማህበራዊ እኩልነት መገለጫ በመሆኑ፣ ሃብቱን በአግባቡ መገምገምና ማስተዳደር ለሀገሪቱ የወደፊት ህልውና ወሳኝ ነው ብለዋል። ​

የመንግስት አገልግሎት ሪፎርሙን ለማሳካት የብቃትና ምዘና ማዕቀፍ ስልጠና ለውሃና ኢነርጂ ዘርፍ አመራሮችና ሠራተኞች ተሰጠ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሥራ አመራር ዋና ሥራ አስፈጻሚና የዘርፉ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የአብይ ኮሚቴ ጸሀፊ አቶ ኦልቀባ ባሼ ሲሆኑ፣ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በሁለተኛው ዙር የሪፎርም ትግበራ ውስጥ ከተካተቱ ተቋማት አንዱ መሆኑን ገልጸዋል።

የአፍሪካ ቻይልድ ሚኒ ግሪድ ፕሮጀክት በሚኒ-ግሪድ ታሪፍ ማስያ መተግበሪያ ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ ነው።

በዉሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በዩኤን ዲፒ የአፍሪካ ቻይልድ ሚኒ ግሪድ ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ይመስላል ተፈራ ስልጠናው በዘርፉ ያሉ የቁጥጥር ማዕቀፎችን፣ ምርጥ ተሞክሮዎች እና የታሪፍ አወሳሰን ስልቶችን ያካተተ ሲሆን ተሳታፊዎች የቴክኒክና የፋይናንስ መረጃዎችን ወደ ስራ በመቀየር ረገድ ያላቸውን እውቀት ያሳድጋል ብለዋ

ተፈትኖ ያለፈው የባስኬት ፈንድ ፕሮግራም

ፕሮግራሙ የተቀረጸው የመጠጥ ውሃ አቅርቦትን በከተሞች የማሳደግ ዓላማ በመያዝ ሲሆን፤ በተበታተነ መንገድ የሚገኘውን የፋይናንስ ድጋፍ በአንድ ቋት በማሰባሰብ በተደራጀ መልኩ ትርጉም ያለው ስራ ለመስራት ነው።

የመጠጥ ውሃ ተቋማት በዘላቂነት አገልግሎት እንዲሰጡ ህብረተሰቡ እንደግል ንብረቱ ሊንከባከብ ይገባል ተባለ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የውሃ ልማት ፈንድ መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ዶጊሶ ጎና የውሃ ልማት ፈንድ ከተቋቋመ 23 ዓመታት ቢሆነውም በረጅም ጊዜ ብድርና በአነስተኛ ወለድ የተገኘ ሀብትን በማስተባበር በውሃ ልማት ዘርፍ በርካታ ስራዎች ሲሰሩ እንደነበር አስታውቀዋል።

ከ227 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የፀሓይ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ዛሬ ያሰመረቅነው ፕሮጀክት ከ227 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት እና ከ2 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን የኤሌክትሪክ ሀይል ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ማኔጅመንት ጋር የባዮጋዝ ማብላያ ፕሮጀክት ወቅታዊ ሁኔታና ቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ውይይት አካሂዷል።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ ከዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት ጋር ፕላንቱ መጀመሪያ ሲገነባ የምርምር ማዕከል እንዲሆን ታሳቢ የተደረገና ከኃይል አቅርቦት ባለፈ ዋነኛ ዓላማው የተፈጥሮ አፈር ማዳበሪያውን በመጠቀም ገቢ መፍጠርና ግብርናን ምርት በማሳደግ የምግብ ሉአላዊነትን ማረጋገጥ ላይ ያተኮረ ነው ብለዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የከርሰ ምድር የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ለማካሄድ የውል ስምምነት ተፈራረመ።

በሚኒስቴር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ ሲሆኑ የውል ስምምነቱ የተፈረመው ከሚድሮክ ጂኦ ኤክስፕሎሬሽን ኃላ.የተ.የግ.ኩባንያ (ደቡብ ኢትዮጵያ አባያ -ጫሞ ሳይት)፣ ከአልባዴ ጠቅላላ ኮንስትራክሽንና የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ኃላ.የተ.የግ.ኩባንያ (ደቡብ ምዕራብ ጊምቦ- ጬና ሳይት) እና ከ

የባስኬት ፈንድ ፕሮግራም 43 ከተሞችን ንፁህ የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የማቺንግ ፈንድ ፕሮግራም እ.ኤ.አ በ2016 ስንጀምር የጋራ ራዕያችን ለማሳካት በፍጥነት በማደግ ላይ ለሚገኙ ትንንሽ እና መካከለኛ ከተሞችን ለማቋቋም ዘላቂ የውሃ እና የንፅህና አጠባበቅ ስርዓት ለመገንባት ያለመ ነበር ብለዋል።

በያንጉዲ ወረዳ የአፈርና ውሃ ጥበቃና የጎርፍ አደጋ መከላከል የልማት ሥራ ለማስጀመር የባለድርሻ አካላት የማኅበረሰብ ንቅናቄ መድረክ ተካሄደ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተፋሰስ ልማትና ጎርፍ መከላከል ዴስክ ኃላፊ አቶ በቀለ ብዙወርቅ የባዘርኔት ፕሮጀክት አንዱ ኮምፖነንት በሆነው የአፈርና ውሃ ጥበቃ እና የጎርፍ መከላከል ሥራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው፣ ፕሮጀክቱ በያንጉዲ ወረዳ የሚታዩ የአፈር መሸርሸር፣ የመሬት መራቆት እና የጎርፍ አደጋዎችን

የውሃ ሀብታችንን በዘላቂነት ለማስተዳደር፣ ለማረጋገጥ እና የዜጎችን የአገልግሎት ጥራት ለማሻሻል ደንበኛን ያማከለ አገልግሎት አሰጣጥን ማጠናከር አስፈላጊ ነው ተባለ።

በውይይት መድረክ ላይ የውሃ ሀብታችንን በዘላቂነት ለማስተዳደር፣ ለማረጋገጥ እና የዜጎችን የአገልግሎት ጥራት ለማሻሻል ደንበኛን ያማከለ አገልግሎት አሰጣጥን ማጠናከር አስፈላጊ ነው ያሉት በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ተቋሙ ለከተማ መጠጥ

በቤዚን አቀፍ የዘላቂነት ማረጋገጫ/BaSRINET/ፕሮጀክት አማካኝነት በንግድና ስራ ፈጠራ ዙሪያ የተሰጠው ስልጠና የሴቶችን ተጠቃሚነት በሚገባ የሚያረጋግጥ ነው - ተሳታፊዎች

የዋቢሸበሌ ባዘርኔት ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ኢሊያስ ሁሴን እንዳመለከቱት ፕሮጀክቱ በአካባቢው አቅዶ ከሚተገብራቸው ቁልፍ ተግባራት መካከል የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት የሚገጥሙ ማህበራዊ ችግሮችን በዘላቂነት መፍታት ዋናው ስራ ሲሆን በስራ ፈጠራና ክህሎት ላይ ተመርኩዞ የተዘጋጀው ይህ መድረክ የሴቶችን የኑሮ ሁኔ

የኢነርጂ ዘርፍ የሚጨበጥ የተስፋ ጉዞ

ኢነርጂ የኢንዱስትሪ መስፋፋት፣ የግብርና ምርታማነት እና የአገልግሎት ዘርፍ ዕድገት ቁልፍ ግብዓት ነው። ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት "የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ማዕከል" ለመሆን በምታደርገው ጥረት የኢነርጂ መሰረተ ልማት ዝርጋታ የሀገሪቱን የሁለገብ ዕድገት ለማፋጠን ወሳኝ ሚና ይጫወታል።

የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት 100 ዘመናዊ የአየር ሁኔታ ጣቢያዎችን ለመትከል የግዥ ውል ፈረመ።

የኢንስቲትዩቱ የትንበያና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አሳምነው ተሾመ እንደገለጹት፣ ጣቢያዎቹ በጎርፍ መከላከል ፕሮጀክቱ በሚተገበርባቸው የአዋሽ፣ የስምጥ ሸለቆ ሐይቆች እና የኦሞ–ጊቤ ተፋሰሶች አካባቢዎች ላይ እንደሚተከሉ ገልጸዋል።

የከተማ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን አገልግሎት ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ለማቋቋም በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ውይይት ተደረገ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የከተሞች የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን አገልግሎት ተቆጣጣሪ ባለስልጣንን ለማቋቋም እየተሰራ ያለውን ሂደት ለማሳወቅ፣ የሚቋቋመው የፌዴራል ተቆጣጣሪ ባለስልጣን አዋጅ ላይ ማብራሪያ ለመስጠት እንዲሁም ባለስልጣኑ ሊጠቀምባቸው በሚችለው መሠረታዊ የቁጥጥር መሣሪያዎች ላይ ስልጠናና

የቤዚን አቀፍ የዘላቂነት ማረጋገጫ ፕሮጀክት ዋቢ ሸበሌ ተፋሰስ በንግድና ስራ ፈጠራ ዙሪያ ለሴቶች የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ ነው።

የሸበሌ ዞን ምክትል አስተዳደር አቶ ኢሴ አብዱላሂ በራኪ በበኩላቸው የቤዚን አቀፍ የዘላቂነት ማረጋገጫ ፕሮጀክት የተለያዩ የልማት ስራዎችን በዘላቂነት ለመፍታትና በዋቢ ሸበሌ ተፋሰስ የአካባቢውን የተፈጥሮ ሃብት የሚያጎለብቱና የሴቶችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስራዎች እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀው የተዘጋጀውን የአቅም ማጎ

በ405 ሚሊዮን ዶላር የሚተገበረው የHCO ፕሮጀክት በ65 ወረዳዎች ውጤታማ ስራዎችን እያከናወነ ነው ተባለ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የHuman Capital Operation ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ሀብተሙ ዱጉማ እንደገለጹት፣ ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ በስተቀር በሁሉም ክልሎች በሚገኙ 65 ወረዳዎች ላይ እየተተገበረ ሲሆን፣ በተለይም የሰው ሀብት ልማት ዝቅተኛ በሆነባቸው፣ በድርቅ ተጽዕኖ በሚደርስባቸው፣ በድንበር አካባቢዎች