Jun 2023

በአካባቢ የሚገኙ የኢነርጂ ምንጮችን በመጠቀም ከዋና መስመር የሚርቁ ቦታዎችን የሀይል ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡

የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ መሰል የአነስተኛ የሀይል ማመንጫ ግንባታ የመሬት አቀማመጡ ሀይል ለማመንጨት ምቹ በሆኑ አካባቢዎች እንደሚቀጥልና በቀጣይ በአማራ፣ በኦሮሚያና በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ ክልሎች ሶሰት የአነስተኛ ሀይል ማመንጫዎች እንደሚገነቡ ገልጸዋል፡፡

May 2023

ንጹህ የማብሰያ ኢነርጂ ቴክኖሎጂን ለማህበረሰቡ ለማስተዋወቅ ለሚዲያ አካላት በዘርፉ የሚሰጠው ስልጠና ጠቃሚ ነው ተባለ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከክሊን ኩኪንግ አሊያንስና ከ ከኔዘርላንድስ የልማት ድርጅት (SNV) ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ለሚዲያ ባለሙያዎች ንጹህ የማብሰያ ኢነርጂ ቴክኖሎጅና ሚዲያን አስመልክቶ ለ5 ተከታታይ ቀናት በቢሾፍቱ ከተማ ስልጠና ሰጥቷል።

በተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ዙሪያ ለደቡብ ብ/ብ/ሕ/ ክልል፣ ለሲዳማ ክልልና ለዞን አመራሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።

ከውሃ ሀብት አስተዳደር ጋር ተያይዞ የህግ ማእቀፎች፣ ስለተፋሰስ እቅድ ምንነትና የውሃ ሀብት አጠቃቀም ተግዳሮቶችና መረጃዎች እንዲሁም የውሃ አካላት ደህንነት ዙሪያ ለደቡብ ብ/ብ/ሕ/ ክልል፣ ለሲዳማ ክልልና ለዞን አመራሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።

በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል ምእራብ ሸዋ ዞን ወልመራ ወረዳ ብርኩሳሜ ቀበሌ ጋቢ ሮቢ ሞዴል የባዮ ጋዝ ዳይጀስተር መንደር ተመረቀ፡፡

የብሄራዊ ባዮጋዝ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ተመስገን ተፈራ በበኩላቸው ፕሮግራሙ በ2030 ዓ.ም. 165 ሺ የሚደርሱ አባዎራዎችን የባዮጋዝ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ለማድረግ በኔዘርላንድስ የልማት ድርጅት (SNV) እና ከመንግስት ጋር በመተባበር እየሰራ መሆኑን ገልጸው የባዮጋዝ ፕሮግራም ከሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ጤናና ማህራዊ

ከባዮጋዝ ሀይል ማመንጨት ከሰርቶ ማሳያ ባለፈ ወደ ግብይት ስርዓት ማደግ እንዳለበት ተጠቆመ፡፡

በሕ/ተወካዮች ም/ቤት የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በመስክ በመገኘት በብሔራዊ ባዮጋዝ ፕሮግራም አስተባባሪነት ከሚተገበሩ ተቋማዊ የባዮጋዝ ፕሮጀክት ጉብኝት ላይ የብሄራዊ ባዮጋዝ አስተባባሪ ኮሚቴ እንደገለጹት የብሔራዊ ባዮጋዝ ፕሮግራም ከተጀመረ ከ15 ዓመት በላይ ማስቆጠሩን ገልጸ

የተፈጥሮ አደጋዎችን ለመከላከል የተጠናከረ የቅድመ ማስጠንቃቂያ ስርዓት መዘርጋት እንደሚገባ ተገለጸ፡፡

በጀኔቫ ስዊዘርላንድ እየተካሄደ በሚገኘው አስራዘጠነኛው የአለም ሜቲሮዎሎጂ ድርጅት ኮንግረስ እየተሳተፉ የሚገኙት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ እንደገለጹት የአየር ንብረት ለውጥ ድርቅ፣ የጎርፍ አደጋ፣ የደን ቃጠሎና የመሬት መንሸራተት የመሳሰሉ ተፈጥ

በአፋር ብሔራዊ ክልል በታችኛው አዋሽ ወንዝ ላይ የተጀመረው የወንዝ አመራር ስራ ተጎበኘ።

የውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ እንደገለጹት በመካከለኛው አዋሽ 3 ወረዳዎች ማለትም ገዋኔ፣ ዱለቻ እና ገልአሎ ከ123 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የወንዝ አመራር ስራ በማከናወን ችግሩን ለመከላከል እየተሰራ መሆኑንና በዚህ ፕሮግራም ተደራሽ ባልሆኑ ሌሎች ወረዳዎች ደግሞ

ኢትዮጵያ እምቅ የታዳሽ ኤሌክትሪክ ሀይል ቢኖራትም እስካሁን ጥቅም ላይ ማዋል የተቻለው5.4 ጌጋ ዋት ብቻ መሆኑ ተገለጸ፡፡

የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር/ኢ/ር ሡልጣን ወሊ በጉብኝቱ ወቅት ለጋዜጠኞች በሰጡት ቃለመጠይቅ ሶላር ኢነርጂን ከማስፋፋት አኳያ እስካሁን በሚፈለገው ልክ ተደራሽ ለማድረግ በመንግስት ሲሰራበት የቆየ ቢሆንም ኢትዮጵያ ካላት የታዳሽ ኢነርጂ 5.4 ጌጋ ዋት ብቻ እየመነጨ መሆኑን ጠቅሰው አሁን ላይ የኢነርጂ

በብድር የተደገፈ የፕሮጀክት አፈፃፀም ሂደት እና የከተሞች መጠጥ ውሃ የብድር ክፍያ ሁኔታ ግምገማ እየተካሄደ ነው።

 የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ እንደገለጹት በሀገራችን ንጹህ የመጠጥ ውሀና ሳኒቴሽን ተደራሽ ማድረግ ጤናማ የሆነ አምራች ዜጋ እንዲኖር ከማገዙም በላይ ሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት እንቅስቃሴዎችን ለማፋጠን ወሳኝ ግብዓትና መሠረተ ልማት መሆኑን አውስተው፤

120 ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ወጭ በኦሞ ወንዝ ላይ እየተከናወነ የሚገኘው የወንዝ አመራር ስራ ተጎበኘ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የሚመራ የከፍተኛ አመራሮችና የባለሙያዎች ቡድን በደቡብ ኦሞ ዞን በዳሰነች ወረዳ በኦሞ ወንዝ ላይ 120 ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ወጪ እየተከናወነ የሚገኘውን የወንዝ አመራር ስራን ጎብኝተዋል።

የበልግ የአየር ንብረት ግምገማ እና የመጪው ክረምት ወቅት የአየር ጠባይ አዝማሚያ ትንበያ ዙሪያ ውይይት ተደረገ ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ እንደገለጹት ባለፉት 3 ወራቶች የተሰጠው የአየር ሁኔታ ትንበያ ሲገመገም የተጣጣመ መረጃ መሆኑንና ከአየር ንብረት ጋር የተያያዙ የጎርፍ አደጋ መሰል ተግዳሮቶችን ለመከላከል ብሎም ለመቀነስ አስተዋጽኦ ማድረጉን ገልጸው፤

በወንጪ ዳንዲ ገበታ ለሀገር የሚገነባ የሙከራ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ውል ስምምነት ተደረገ፡

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ እንዳሉት ይህ የሙከራ ውል የሚገኘውን የውሃ መጠን መነሻ በማድረግ ግምገማ ከተደረተገበት በኋላ ውጤቱን በማየት ሌሎች አራት ተጨማሪ ጉድጓዶች የሚቆፈሩ መሆኑንና የውሃ መስመር የመዘርጋት ስራውም በየደራጀው የሚሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡

የታችኛው አዋሽ ወንዝ የጎርፍ አደጋ ስጋትን ለመቀነስ የሚያስችል ከ43 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የሚደረግበት የወንዝ አመራር ስራ የውል ስምምነት ተደረገ፡፡

የውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ የአዋሽ ወንዝ በተደጋጋሚ በአካባቢው ማህበረሰብ ላይ አካላዊና ቁሳዊ ጉዳት እያስከተለ እንደሚገኝና ይህንንም ወደ ነበረበት ለመመለስ ከአሁን በፊት በተያዘው ዓመት ሚያዚያ ላይ በላይኛው አዋሽ ወንዝ ላይ የወንዝ አመራር ስራ ውል ተወስዶ እየተሰራ

ከዋናው የሀይል መስመር ውጭ (ሚኒ ግሪድ) ኢንቨስትመንት ላይ የሬጉላቶሪ ማእቀፍን አስመልክቶ ውይይት ተካሄደ፡፡

የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ እንደገለፁትበዘርፉ የሚደረጉ ኢንቨስትመንቶችን የሚደግፍና እና የሚያበረታታ የህግ ማዕቀፍ መኖሩ መሠረታዊ መሆኑን ገልፀው በ2012 መጨረሻ ላይ የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን የፈቃድ አሰጣጥን፣ ታሪፍን፣ የቴክኒክ እና የአገልግሎት ደረጃዎችንና ሌሎች

ከ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚገነባ የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት የኮንትራት ውል ተፈረመ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በፊርማ ስነስርዓቱ ላይ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ በሱማሌ ብሔራዊ ክልል ሊበን ዞን ጉራዳሞሌ ወረዳ የሚተገበር ሲሆን፤ ፕሮጀክቱ ለድርቅ ተጋላጭ የሆነ አከባቢ የሚገነባ የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት ሲሆን በተቀመጠው ጊዜ፣ ወቅቱ፣ በጥራትና በልዩ ትኩረት እንዲከናወን አሳስበዋል፡፡

በንፁህ ውሃ አቅርቦት እና በንፅህና አጠባበቅ ላይ በኔዘርላንድ ሄግ ከተማ ሲካሄድ የነበረው የምክክር መድረክ ተጠናቀቀ

የጉባኤው ዋና ዓላማ እ.ኤ.አ ከማርች 22 – 24 በአሜሪካ ኒውዮርክ ሲካሄድ የሰነበረውን የተመድ የውኃ ጉባኤ ማጠቃለያ መርሃ ግብር እና የዘላቂ ልማት ግቦች ቀሪ ስራዎች ላይ መነሻ በማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይቶች እንዲኖሩ ያለመ ነው፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጥልቅ የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ውል ስምምነት ተፈራረመ።

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ በቦረና ዞን በተደጋጋሚ ድርቅ በሚከሰትባቸው አካባቢዎች ድርቁን ለመቋቋም ታሳቢ የተደረጉ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑንና ለአየር ንብረት የማይበገር የውሃ ልማት ስራ ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከ84 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍልን ተጠቃሚ የሚያደርግ የመጠጥ ውሃ ግንባታ የኮንትራት ውል ተፈራረመ፡፡

ክቡር  ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ ኮንትራክተሩ ወደ ስራ ከተገባ በኋላ የሚኖሩ ተግዳሮቶችን እና የአካባቢውን ችግር በሚገባ ተረድቶ በልዩ ትኩረት እንዲሰራ ሲሉም አሳስበዋል፡፡

Apr 2023

የታዳሽ ኢነርጂ ሀብት ለመጠቀም የሚያስችል የቴክኖሎጂ እና የፋይናንስ ተግዳሮቶች ላይ መስራት እንደሚገባ ተገለጸ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ እንደገለጹት አፍሪካ የተፈጥሮ ሀብት ባለቤት መሆኗንና ለማሳያም በኢትዮጵያ እና ታንዛኒያ በታዳሽ ኢነርጂ ሀይል የማመንጨት ከፍተኛ አቅም እንዳላቸው ገልፀው

የሩሲያ የኢነርጂ ካምፓኒ ሩስሀይድሮ በኢትዮጵያ ኢነርጂ ልማት ዘርፍ ለመሰማራት ያለውን ፍላጎት ገለጸ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ እንደገለጹት በሀገሪቱ እምቅ የታዳሽ ሃይል የማምረት አቅም ቢኖርም የኢነርጂ አቅርቦቱ ከ50% በታች መሆኑን ገልፀው፤የኢነርጂ አቅርቦቱን ለማሳደግና በቀጠናው የተጀመረውን የሀይል ትስስር ለማስፋፋት ኢነርጂ የማምረት፣ የማሰራጨትና የማስተላለፍ አቅም ማሳደግ አሰፈላጊነትን አመላክተዋል፡፡

የትንሳኤ እና የኢድ-አልፈጥር በዓላትን ምክንያት በማድረግ የማዕድ ማጋራት መርሃግብር ተካሄደ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በበዓል ወቅት መሰል ተግባራት ሲከናወን የመጀመሪያ እንዳልሆነ ገልፀው እንደአንድ ቤተሰብ አብሮ ማእድ መጋራት ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን የሚያጠናክር በመሆኑ

በተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።

መርሀ ግብሩን በንግግር የከፈቱት በውሃና ኢነርጅ ሚኒስቴር የአባይ ቤዚን አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ የወንደወሰን መንግሥቱ እንደገለጹት የአባይ ቤዚን ፕላን ሲዘጋጅ ለሀገራችን አዲስ ሀሳብ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በርካታ ተግዳሮቶች እንደነበሩ ጠቅሰው ችግሮቹን ለመፍታት አለም አቀፍ ተሞክሮዎችን በመቀመር

8ኛው የውሃ፣ የውሃ ዲፕሎማሲና ኮሙኒኬሽን ፎረም ተጠናቀቀ፡፡

የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ እንደገለፁት ከዚህ ቀደም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ እና በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉን ግንዛቤ የሚያሳድጉ ስራዎች መቅረባቸውንና በእለቱም ተመሳሳይ ስራዎች መቅረባቸውን ገልጸዋል።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከአለም ባንክ የውሃ ዘርፍ ዳይሬክተር ሳሮጅ ኩማር እና ልኡካን ቡድናቸው ጋር ተወያዩ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የዘርፉን ፖሊሲ ከመከለስና አዲስ ተቋማዊ መዋቅር ከማዘጋጀት ጀምሮ በየደረጃው ያሉ የውሃ ባለሙያዎችን አቅም በመገንባት ሰፋፊ ሥራዎች እየተሰሩ ቢሆንም በግብዓት አቅርቦት ላይ የሚታየው የዓለም የገበያ ዋጋ ንረት፣ የግዥ ሂደት መጓተት፣ ከመፈጸም አቅም፣ ከአየር ን

የኮሙኒኬሽን ባለሙያዎችን አቅም የመገንባት ተግባር በትኩረት መሰራት እንዳለበት ተገለፀ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ለክልሎች ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም ለተጠሪ ተቋማት የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና በትኩረት ሊሰራበት እንደሚገባ ተገለጸ፡፡

ለተጠሪ ተቋማት እና ለክልል ውሃና ኢነርጅ ቢሮዎች የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጠ ፡፡

የስራ አመራር ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ኦልቀባ ባሼ ወቅቱንና ጥራቱን የጠበቀ መረጃዎችን በማደራጀት በተለያዩ የኮሙዩኒኬሽን ቻናሎች ተጠቅሞ ለሚመለከተው አካል ተደራሽ ለማድረግ ተቋማዊ የማስፈጸም አቅም ማሳደግ ያስፈልጋል ብለዋል።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በጀርመን ከሚገኘው የሚሲዮኑ ሰራተኞች፣ የልማት አጋር ድርጅቶችና ባለሀብቶች ጋር ውይይት አካሄዱ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በጀርመን በርሊን በሚገኘው የኢትዮጵያ ሚሲዮን ሰራተኞች ጋር በአሁናዊ ሀገራዊ ጉዳይና የአጋር ድርጅቶችን ትብብር በሚጠይቁ የመሰረተ ልማት ፕሮግራሞች ዙሪያ ሰፊ ውይይት አደርገዋል፡፡

የጎርፍ አደጋን ለመከላከል የሚያስችል የወንዝ አመራር ተግባራትን ለማከናወን የኮንትራት ውል ስምምነት ተፈራረመ፡፡

ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ የውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ የተጣለበትን ኃላፊነት ለመወጣት ከመንግስት መደበኛ በጀት በተገኘ ገንዘብ የጎርፍ አደጋ ስጋት ታሳቢ ያደረገ የመፍትሄ እርምጃ ለመውሰድ ብሎም በተደጋጋሚ የጎርፍ አደጋ የሚከሰትባቸውን አካባቢዎች በውስጥ አቅም ጊዜያዊ መፍትሄ ለመስጠት ታላሚ ያደረገ መሆኑን ገለፁ

ለሃይል ልማት የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ አስፈላጊ መሆኑ ተገለጸ፡፡

በጀርመን በርሊን ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የበርሊን ኢነርጂ ትራንዚሽን ዲያሎግ ላይ የተገኙት ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የኢነርጂ ሀብት ልማት በመንግስት ወጪ ብቻ መሸፈን የማይቻል እና የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በእጅጉ የሚሻ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

Mar 2023

ተቋሙ ከኦሮሚያ ውሃና ኢነርጂ ቢሮ ጋር በመተባበር በተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ዙሪያ ስልጠና አካሄደ።

ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ እንዳሉት ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ሚኒስቴር መሥርያ ቤቱ ተቋማዊ ሪፎርም መደረጉን አስታውሰው የሀገሪቷን የውሃ ሀብት በተገቢው መንገድ ጥቅም ላይ ማዋል፤ ዘመናዊ የውሃ ሀብት አስተዳደር ሥርዓት ማስፈን፤ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና የሳኒቴሽን አገልግሎት ተደራሽነት ማስፋፋት እና የኢነርጂ ልማት ማ

የሶላር ኢነርጂን በመጠቀም የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ አማራጭ መሆኑ ተገለጸ፡፡

የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር/ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ከሰሞኑ በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በተለያዩ ቀበሌዎች በመዘዋወር ምርታማነትን ለመጨመር እየተተገበረ ያለውን የሶላር ማቀዝቀዣ የሙከራ ፕሮጀክት ጎብኝተዋል፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በኒውዮርክ እየተካሄደ በሚገኘው የተባበሩት መንግስታት የውሃ ጉባዔ ተሳተፉ፡፡

የጉባዔው  ዋና የመወያያ ርእሰ ጉዳዮች ውሃ ለጤና፤ ውሃ ለዘላቂ ልማት፤ ውሃ ለአየር ንብረት እና አካባቢ፣ ውሃ ለትብብር የመሳሰሉት ሲሆኑ፤ በሶስት መድረኮች ማለትም፤ ውሃ ለዘላቂ ልማት፤ ውሃ ለአየር ንብረት እና አካባቢ እና ውሃ ለትብብር በሚሰኙት መድረኮች ላይ የኢትዮጵያ ልኡካን ንግግር እንደሚያደርጉ ይጠ

በ60 ሚሊየን ብር ወጪ መልሶ የተገነባው የመጠጥ ውሃ ተቋም አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ የፌደራል መንግሰት በጦርነት የተጎዱ የሀገራችን አካባቢዎች ላይ በተለያየ መንገድ እየደገፈ መሆኑን ገልጸው የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴርም የንጹህ መጠጥ ወሃ አቅርቦት ላይ የመልሶ ግንባታ እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የከተማ የውሃ አቅርቦት ጥናት፣ የዲዛይን፣መመዘኛ እና መለኪያ ጋይድ ላይን ላይ ምክክር ተደረገ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ የውሃ አቅርቦት ሽፋንን በማስፋፋት ደረጃውን የጠበቀ እና ንጽህናው የተረጋገጠ የውሃ አቅርቦት ለህብረተሰቡ ለማዳረስ የከተማ ውሃ አቅርቦት ጥናት፣ የዲዛይን፣መመዘኛ እና መለኪያ ጋይድላይን ችግር ፈቺ እንደሚሆን ጠቁ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ከጀርመን የልማት ድርጅት (GIZ) ተወካዮች ጋር ተወያዩ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ የኢትዮጵያና ጀርመን ግንኙነት እድሜ ያስቆጠረ ግንኙነት መሆኑን አውስተው በተለይ፤ የጀርመን የልማት ድርጅት በኢነርጂ ልማት ዘርፍና በሌሎች መስኮች አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ከቻይና አለምአቀፍ የኢነርጂ ቡድን ሊቀመንበር ጋር ተወያዩ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ እንደገለጹት ባለፉት አመታት የቻይና ካምፓኒዎች በመሰረተልማት ግንባታ ዘርፍ ከፍተኛ ተሳትፎ ማድረጋቸውን ጠቅሰው ኢትዮጵያ በኢነርጂ ዘርፍ በርካታ የኢንቨስትመንት እድሎች መኖራቸውን ገልጸዋል፡፡

በየደረጃው ያለውን አመራር አቅምን መገንባት ተቋማዊ ራዕዩን እውን ለማድረግ አስተዋጽኦ እንዳለው ተገለጸ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሡልጣን ወሊ እንዳሉት ተቋሙ በርካታ የአቅም ግንባታ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱንና እየሰራ እንደሚገኝ አውስተው በእያንዳንዱ ዘርፍ የሚሰሩ ስራዎችም የአቅም ግንባታውን የሚያበለጽጉ ናቸው ብለዋል፡፡

127ኛው የአድዋ ድል በዓል ተከበረ።

የውሃ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር አብርሃ አዱኛ የአደዋ ድል ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለመላው ጥቁር ህዝብ ኩራት ፣ የነጻነት ተምሳሌት መሆኑን ብሎም ጣሊያንን በማሸነፍ ሂደት በአለም አደባባይ ቀና ብለን እንድንሄድ ከማድረጉም በላይ የሴቶች የአመራር ጥበብ የታየበት ድላችን ነው ብለዋ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በቦረና ዞን በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ አደረገ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከውሃ ማልማትና አቅርቦት ጋር ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰራና የተጓተቱ ፕሮጀክቶችን በተፋጠነ ሁኔታ በማስተካከል በሁለት አመት ውስጥ ውጤታማ ለማድረግ እንሰራለን ብለዋል።