Dec 2025

በሃዋሳ ከተማ ለሚገነባው ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያና ማስወገጃ ፕሮጀክት (Faecal Sludge and Septage Treatmenet Plant ) ግንባታና ጥገና የውል ስምምነት ተፈረመ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከአለም ባንክ በተገኘ የብድር ድጋፍ በ23 ከተሞች የሚተገበር የሁለተኛው የከተሞች መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት አካል የሆነው በሃዋሳ ከተማ የሚገነባው ዘመናዊ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ እና ማስወገጃ ፕሮጀክት የኢትዮጵያ መንግስት ከተሞችን ጽዱ፣ ማራኪ እና ውብ ለማድረግ እያከናወነ ያለ

ለሕዝባችን ሁለንተናዊ የውሃ አቅርቦትና የንፅህና አጠባበቅ ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ከገንዘብ ድጋፍ በላይ ውጤታማ አፈፃፀም በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑ ተገለጸ።

ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ፒ..ኤች.ዲ) ባለፉት 3 ዓመታት የፕሮጀክቱን የአፈጻጸም ሂደት ለመገምገም እና በቀሪ ሦስት ዓመታት የፕሮጀክቱን ዓላማ ለማሳካት ለሚመጡት 3 ዓመታት የፕሮጀክት ትግበራ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫ ለማስቀመጥ መንግስትን እና ዓለም ባንክን የሚያጣምረው ይህ የግምገማ መድረክ ወሳኝ ምዕራፍ መሆ

በምንሰራው ስራ ሁሉንም ተጠቃሚ ሰናደርግ የምናከብረው በዓል ውጤታማና ትርጉም ያለው ይሆናል ሲሉ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ገለጹ።

20ኛውን የብሄር ብሄረሰቦች ቀን ''ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረብሄራዊ አንድነት'' በሚል መሪ ቃል በተከበረበት ወቅት ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በምንሰራው ስራ ሁሉንም ተጠቃሚ ሰናደርግ የምናከብረው በዓል ውጤታማና ትርጉም ያለው ይሆናል ብለዋል።

በዋቢ ሸበሌ ተፋሰስ ተግባራዊ ለሚደረገው የተቀናጀ ስራ ምቹ ሁኔታ መኖሩ ተገለጸ።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከሰሞኑ በዋቢ ሸበሌ ተፋሰስ በባዘርኔት ፕሮጀክት ተግባራዊ የሚደረገውን የተቀናጀ ስራ የነባራዊ ሁኔታ ግምገማ ሪፖርትን ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን ይህንን አስመልክቶ ለስራው የተመረጡ አካባቢዎች ተጎብኝተዋል።

ከ299 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የሲቪል ስራና የኤሌክትሮመካኒካል መስመር ዝርጋታ የውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የኢዋያ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በቦረና አካባቢ እንደሚገኝ ገልፀው አካባቢው በከፍተኛ ሁኔታ ውሃ አጠርና ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ በድርቅ የተጠቃ አካባቢ በመሆኑ ስራው ህብረተሰቡን ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ በፍጥነትና በጥራት መሠራት አለበት ብለዋል።

ከ156 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ለ44 ከተሞች የውሃ አገልግሎት ጽ/ ቤቶች የቁሳቁስ የአቅም ግንባታ ድጋፍ ተደረገ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ የቁሳቁስ ድጋፉ የተደረገው በ7 ክልሎች በ44 ከተሞች የውሃ አገልግሎት ጽ/ቤቶችን አቅም ለማጎልበት፣ አገልግሎቱን ለማዘመንና ለማሳለጥ እንደሚየግዝ ታስቦ ነው ብለዋል።

በ15 ሚሊዮን ብር የተቀናጀ የመረጃ ሲስተም ለማልማት ሶፍትዌር ከሚያለማ ድርጅት ጋር የውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ የውሃልማት ፈንድ ብድር አስተዳደር በዘመናዊ ቴክኖሎጂና ደረጃውን በጠበቀ የመረጃ አያያዝ በአይቲ /Information Technology/ መደገፍና ሲስተሙ መዘርጋት ስላለበት የውልስምምነቱ አስፈልጓል ብለዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ክቡር ዶክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ ሙስናን ለመከላከል መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ ባከናወነው ተግባር ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገለጹ

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ሙስና ለዘመናት የሀገር ዕድገት ማነቆ ሆኖ ቆይቷል፤ ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ ሙስናን ለመከላከል መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ ባከናወነው ሰፊ ተግባር ውጤት መመዝገቡን ተናግረው ለዚህም ውጤት መመዝገብ በዋነኝነት የሚጠቀሠው የተቋማት አሠራር በሪፎርም እንዲቃኝ መደረጉ እንደሆነ ገልፀዋል

በባዘርኔት ፕሮጀክት የሚተገበረው የዋቢ ሸበሌ ተፋሰስ የነባራዊ ሁኔታ ግምገማ ሪፖርት ላይ ውይይት ተደረገ።

የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ውሃን በተመለከተ በርካታ ስራዎችን እየሠራ እንደሚገኝ ገልጸው ባለፉት ሶስትና አራት አመታት የውሃው ዘርፍ በራሱ ተደራጅቶ እንዲመራ መደረጉ ለውጤቱ አስተዋጽኦው የጎላ ነው ብለዋል።

ከ48 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ከኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ጋር የአቅም ግንባታ ስልጠና ውል ስምምነት ተደረገ፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ስምምነቱን በፈረሙበት ወቅት ሚኒስቴር መ/ቤቱ በገጠርና በከተማ በተለያዩ አካባቢዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚሰራው የአቅም ግንባታ ስራ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ የኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ለብዙ አመታት ያካበተውን አቅም በመጠቀም ብቃት ያላቸውን ባለሞያዎችን ለማፍራት ስት

Nov 2025

በኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ልማትፕሮጀክት የሩብ ዓመት የግምገማ ሪፖርት ቀረበ

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ለማት ፕሮጀክት በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች በተደጋጋሚ ከሚጠቁ አምስት የአፍሪካ አገራት የመጠጥ ውሃ እና መስኖ ልማት ዋነኛ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት ከዓለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ አካባቢያዊ እና ማህበራዊ የል

የውሃ ሀብት አጠቃቀምንና ፈቀቃድ አሰጣጥን ማዘመን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ተገለፀ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከክልል ውሃ ቢሮዎች፣ ከቤዚን አስተዳደር ፅ/ቤቶች፣ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤት እና ከተለያዩ ፕሮጀክቶች ተወክለው ከመጡ ሀላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር የውሃ ሀብት አጠቃቀምና ፈቃድ አሰጣጥን ማዘመንና /E-Service/ አሰጣጥ ላይ ስልጠና ተሰጥቷል።

በክትትልና ግምገማ እና የመማማር ማዕቀፍ ረቂቅ ሰነድ ላይ ውይይት ተካሄደ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በፕሮጀክቶች ሳይት ዙሪያ ድጋፍና ክትትል በሚደረግበት ወቅት ኮንትራክተሮች ምን እንደሚሰሩ በጥልቀት መመርመር፣ አማካሪዎች ሚናቸውን በአግባቡ መወጣታቸውን መቃኘትና የመስሪያ ቤቱን አቅርቦት መፈተሽ ይገባል ያሉ ሲሆን እስከ ነሀሴ ወር መጨረሻ እያንዳንዱ ፕሮጀክት ያከናወናቸውን ተግባራት

ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተገነባ ያለው ለገጣፎ ለገዳዲ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተጎበኘ።

በውሃ ልማት ፈንድ እያስገነባቸው ከሚገኙት የመካከለኛ ከተሞች መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ እና ከ5000ሜትር ኩዩብ ውሃ የማጠራቀም አቅም ያለውን የለገጣፎ ለገዳዲ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክት ያለበትን ደረጃ የምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አባላትን ያስጎበኙት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አመራሮች ፕሮጀክቶቹ በተሻለ

ከ839 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የከርሰ ምድር ውሃ ሀብት አለኝታ ልየታና ልማት የመጠጥ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ውል ስምምነት ተፈረመ፡፡

በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ ፕሮጀክቱ የምስራቅ አፍሪካ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት አካል ሲሆን በ240 ቀናት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ ገልጸዋል፡፡

ወደ ሪፎርም መግባት ጊዜው የሚጠይቀው ተግባር መሆኑ ተገለጸ።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንደ ሀገር በሁለተኛው ዙር ወደ ሪፎርም ከገቡ ተቋማት አንዱ መሆኑን የገለጹት አቶ ማሙሻ ሪፎርሙን በውጤታማነት ለመፈጸም በየደረጃው አብይ ፣ ቴክኒካል እና ንኡሳን ኮሚቴዎች ተዋቅረው ወደ ተግባር ተገብቶ በርካታ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የድጅታል አሰራር ስርዓቱ የተለየ ተነሻሽነት ፈጥሯል ሲሉ የናይጄሪያ ቡድን አባላት ተናገሩ።

ባለሞያዎቹ ከሚኒስቴር መ/ቤቱ ጋር የልምድ ልውውጥ ለማድረግ የመጡ ሲሆን በነበረው ውይይት በውሃ ሀብት አስተዳደር፣ በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን እና በኢነርጂ ልማት ዘርፍ የሚከናወኑ ስራዎች ዙሪያ ገለፃ ተደርጎላቸዋል።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ከተለያዩ ለጋሽ ድርጅቶች ተወካዮች ጋር ተወያዩ።

ክቡር አምባሳደር በውይይቱ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና የሳኒቴሽን መሰረተ ልማት ግንባታ እና ዘለቄታዊ አገልግሎትን አስመልክቶ ከጤና፣ ከትምህርትና ከገንዘብ ሚኒስቴር መ/ቤቶች ጋር በጋራ እየሰሩ እንደሆነ ገልፀው፤ በአሀዳዊ ዋሽ ብሔራዊ ፕሮግራም ንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና የሳኒቴሽን መሰ

ለሁለንተናዊ ጤና ውሃና የውሃ አስተዳደር ሚና ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ።

ከዓለም የውሃ ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት /Internationale water management institute/፣ከጤና ሚኒስቴር እና ከሌሎችም ባለድርሻ ተቋማት ጋር በትብብር በተዘጋጀው መድረክ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተቀናጀ ውሃ ሀብት አስተዳደር ዋና ስራአስፈፃሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ ለሁለንተናዊ ጤና ውሃና የውሃ አስተ

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የባዘርኔት ፕሮጀክት የአቅም ግንባታ ስልጠና እያካሄደ ነው

የተቀናጀ የውሃ ሃብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ እንደገለጹት ስልጠናው በጂኦሎጂካል ኢንፎርሜሽን መረጃ ትንተናና በመሬት ቅኝት ዙሪያ የሃገራችንን ወሳኝ የሆነ ቴክኖሎጂ ለማስተዋወቅ የሚጀመርበት መርሃ ግብር መሆኑን ገልጸዋል ፡፡

ከ202 ሺ ዪሮ በላይ በሆነ ወጪ የማማከር አገልግሎት የውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ ኢትዮጵያ ዘመናዊ አሰራርንና መረጃ አያያዝን ተግባራዊ እያደረገች ባለበት በዚህ ወቅት ከአሜሪካው አጎጊ ድርጅት ጋር የስራ ውል መግባቱ ጥሩ አጋጣሚ መሆኑን ገልፀው እድሉን ስላገኙ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

ክቡር ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የሱዳን አምባሳደር እና የአፍሪካ ህብረት ቋሚ ተወካይ አምባሳደር አል-ዘይን ኢብራሂምን በፅ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ በውይይታቸው ኢትዮጵያና ሱዳን የቆየ የሁለትዮሽ የግንኙነት ታሪክ እንዳላቸው ገልፀው፤ በሱዳን መንግስት በኩል በኢነርጂው ዘርፍ ከኃይል አቅርቦት ጋር ስላለው ግንኙነት አብራርተዋል፡፡

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍ ላይ የጋራ ግንዛቤ ሊኖር ይገባል ተባለ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በክቡር ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ሀይሌ ሪፎርሙን አስመልክተው ለተቋሙ ሰራተኞች ሰፊ ገለፃ እንደተሰጠ አስታውሰው፤ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም በተቋማችን እንዴት መተግበር እንዳለበት የምናይበት ሰነድ ነው ብለዋል።

ተፈጥሮን መሰረት ያደረገ የኢንዱስትሪ ፍሳሽ ቆሻሻን የማጣራትና መልሶ የመጠቀም የውሃ ጥራት መቆጣጠሪያ ቴክኖሎጂ ውጤታማ መሆኑ ተገለፀ።

አዲሱን ቴክኖሎጂ ተጠቅመው ወደ ውሃ አካላት የሚለቀቀውን ፍሳሽ ተጣርቶ መለቀቁንም በየጊዜው በባለሞያዎች ክትትል ይደረጋል ያሉት አቶ መንበሩ፤ የቀይ ቡና መፈልፈያው ድርጅት የውጪ ምንዛሪ ከማስገኘቱም ባሻገር ለሴቶችና ወጣቶች የስራ ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል።

ከ 4.6 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ በአዳማ እና በባህርዳር ከተማ የፍሳሽ ማጣሪያና ማስወገጃ ግንባታ ውል ስምምነት ተደረገ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ፕሮጀክቱ ትልቅ በመሆኑ በቁርጠኝነት ከውሃ አገልግሎት እና ከክልል ውሃ ቢሮዎች ጋር ሀብትን በአግባቡ መጠቀም ላይ ትኩረት በማድረግ እንዲሰሩ አሳስበዋል፡፡

በፈረንሳይ የአማካሪ ልማት ድርጅት በተጠናው የከተሞች ቅድመ መለያ መስፈርት እና የአዋጭነት የጥናት ሰነድ ላይ ውይይት እየተደረገ ነው፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ በማከል የውሃ ልማት ፈንድ ከተቋቋመበት አላማ በፖሊሲ ከተቀመጠው የከተሞች ኢኮኖሚማና ማህበራዊ ሀብት ውስጥ አንዱ እና ሰብአዊ መብትም ጭምር በሆነው ንጽህናው የተጠበቀ ውሃ ለህብረተሰቡ ማድረስ ሲሆን በዚህ ደግሞ በከተሞች አካባቢ ብርድ በመስጠት እንዲተገብሩት እየሰራ የሚገኝ ሲ

የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የዝግጅት ምእራፍ ስራዎች በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ ነው፡፡

እንደ ሀገር ወደ ሪፎርም ከገቡ ተቋማት መካከል የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ አንዱ ሲሆን ዘርፉ በኢኮኖሚያዊ ፣ በማህበራዊ እና ፖለቲካዊ እድገት የሚጠበቁበትን ግቦች ለማሳካት የሰው ሀብት ትልቁን ድርሻ ስለሚይዝ ይህ ሀብት የሚመራበት ስርዓት በብቃት ላይ የተመሰረተ እንዲሆን የአገልግሎት አሰጣጡንም ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ

በክቡር ሚኒስትሩ የሚመራው ሉካን ቡድን የመስክ ምልከታ አካል የሆነውን የሰመራ ከተማ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ ፕሮጀክት ያለበት ሁኔታ ምልከታ አደረገ;;

በውይይቱ ላይ ክቡር ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ፕሮጀክቱ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ውስጥ ጥራቱን በጠበቀ መልኩ እንዲጠናቀቅ አሳስበዋል።

ቤዚን አቀፍ ዘላቂነት ማረጋገጫ /BaSRINET/ ፕሮጀክት የአዋሽ ቤዚን ፕሮጀክት ይፋዊ ማስጀመሪያ መርሀግብር ተካሄደ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በኢትዮጵያ የተፋሰስ ስራ የተጀመረው በአዋሽ ተፋሰስ ላይ እንደነበረና ተፋሰሱ ከዚህ በፊት በጎርፍ ምክንያት የዜጎች የመፈናቀልና የችግር መንስኤ ሆኖ መቆየቱን አውስተው አሁን ግን በፕሮጀክቱ በተሰሩ ስራዎች ለአካባቢው ህብረተሰብ እፎይታና የኢኮኖሚ ምንጭ መሆን ችሏል ብለዋል።

ጎርፍን ከስጋት ወደ በረከት መለወጥ እንደሚቻል ተገለፀ

ክቡር ዶ/ር ኢንጅነር ሀብታሙ ኢተፋ በአፋርክልል በአሚበራና ዱለቻ ወረዳ ባደረጎት የሥራ ይፋዊ ጉብኝት በባለፉት ሁለት ዓመታት በአዋሽ ወንዝ ላይ በተሰሩ የ255 ኪሎ ሜትር የጎርፍ መከላከያና የወንዝ አመራር ስራዎች ጎርፍን ከስጋት ወደ በረከት መለወጥ እንደተቻለ ገልፀዋል፡፡

በሶላር ሚኒግሪድ ዝርጋታ ፣ጥገናና አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የሰለጠኑ ሰልጣኞች የብቃት ምስክር ወረቀት ተሠጠ።

የዩኤንዲፒ ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ይመስላል ተፈራ ኢትዮጵያ በሶላር ኢነርጂ የታደለች በመሆኗ ይህን ዕምቅ የሶላር ሀይል በበቂ ሁኔታ ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ሚኒስቴር የመስሪያ ቤቱ በዘርፉ የሚታየውን የብቃት ክፍተት በጥናት በመለየት ክፍተቱን ለመሙላት ስልጠናው ተዘጋጅቷል ብለዋል።

በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ዙሪያ የከርሰ ምድር ውሀ ሀብት አለኝታ ልየታና ልማት የሚውል የ11 የጉድጓድ ቁፋሮ ውል ተፈረመ

ክቡር ዶ/ር ኢንጅነር ሀብታሙ ኢተፋ በተለያዩ ምክንያቶች መጓተት ካለ ለማህበረሰቡም ለኮንትራክተሩም አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚኖረው በማስገንዘብ፤ ችግሮች ካጋጠሙ በወቅቱ በመናበብ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር እንዲሚድረግ አረጋግጠዋል።

በሚኒግሪድ ሶላር ኢነርጂ አቅርቦት ለሚሰማሩ የግል አልሚዎች የብድር አቅርቦት ለማመቻቸት እገዛ የሚያደርግ ስልጠና መመቻቸቱ የሚበረታታ መሆኑን ተሳታፊዎች ገለጹ

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በዩኤንዲፒ ፕሮጀክት አማካኝነት በሶላር ሚኒ ግሪድ ተከላ ስራ በሚሰሩ ስራዎች የግል አልሚዎችን ተሳትፎ ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የግል ባንኮችና ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት የብድር አቅርቦት ለማመቻቸት እንዲችሉ ለአስፈፃሚ አካላት በተሰጡት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ነው።

በዩኤንዲፒ ፕሮጀክት ለተመረጡ ባንኮችና ማይክሮፋይናንስ ተቋማት ስልጠና እየተሰጠ ነው

የዩኤንዲፒ ፕሮጀክት ማናጀር አቶ ይመስላል ተፈራ እንደገለጹት የግልና የመንግስት ባንኮችና ማይክሮፋይናንስ ተቋማት በሚኒግሪድ ዙሪያ ግንዛቤ ለማስጨበጥና በፕሮጀክቱ በሚሰሩ የሶላር ሚኒግሪድ ትግበራዎች ለግል አልሚዎች የብድር አቅርቦት በማመቻቸት ትብብር እንዲያደርጉ ነው ብለዋል፡፡

ከ611 ሚሊዬን ብር በላይ በሆነ አጠቃላይ ወጪ የመጠጥ ውሃ ግንባታና የውል አስተዳደር የማማከር ስራ የውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ ጨረታውን አሸንፈው የውል ስምምነቱን የፈረሙት ድርጅቶች ከሚንስቴር መስሪያ ቤቱ ጋር ከዚህም በፊት የተለያዩ የማማከርና የግንባታ ስራዎችን በውጤታማነት ሰርተው ማስረከባቸውን አውስተው አሁንም የክልሉን ህዝብ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ በሚያደርግ መልኩ በፍጥነትና በጥራት በመስራት

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የፕሮጀክት ግንባታ ለማከናወን ተስማማ

ክቡር ዶ/ር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋ ፤ የድሬዳዋን ህዝብ በፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ለማድረግ ዮት ኮንስትራክሽን በሚፈለገው የጥራት ደረጃና በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ስራውን አጠናቅቆ እንዲያስረክብ አሳስበዋል፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከ2 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የፕሮጀክት ግንባታ ለማከናወን ስምምነት ፈጸመ ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የህብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ በተገባው የውል ስምምነት መሰረት በሚፈለገው የጥራት ደረጃና ከተቀመጠው የጊዜ ገደብ ባጠረ ጊዜ ስራውን እንዲያጠናቅቁ አሳስበዋል።

2ኛው የኢትዮጵያ ውሃና ኢነርጂ ሳምንት ላይ ለተሳተፉ የልማት አጋሮችና የግል ድርጅቶች ዕውቅና በመስጠት ተጠናቀቀ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተዘጋጀው 2ኛው የውሃና ኢነርጂ ሳምንትን አስመልክቶ በኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየም ተዘጋጅቶ በነበረው አውደ ርዕይ ላይ አስተዋፅኦ ላበረከቱ የልማት አጋሮችና እና የግል ድርጅቶች እውቅና ተሰጠ።

መጪው ትውልድ ስለሀገራችን ውሃ ሀብት ግንዛቤ እንዲኖረው ሊሰራ ይገባል ተባለ።

የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ዶ/ር ሚካኤል መሃሪ እንደገለፁት በክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ አነሻሽነት የተጀመረው የውሃ፣ የውሃ ዲፕሎማሲና ኮሙኒኬሽን ኮንፈረንስ ከአምስት አመት በፊት የተጀመረ መሆኑን አስታውሰው፤ በድንበር ተሻጋሪ የውሃ ሀብት ላይ ውይይት፣ መግባባትና ትብብርን ማጎልበት እንደሚገባ ገልፀዋል።

በድንበር ተሻጋሪ ወንዞቻችን ጉዳይ ኢትዮጵያ ያላት ጽኑና የማይቀር አቋም የቀጠናውን ተገቢ፣ ሚዛናዊና ፍትሀዊ የውሃ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ነው ተባለ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በድንበር ተሻጋሪ ወንዞቻችን ጉዳይ ኢትዮጵያ ያላት ጽኑና የማይቀር አቋም የቀጠናውን ተገቢ፣ ሚዛናዊና ፍትሀዊ የውሃ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ነው ብለዋል።

በውሃ፣ በሳኒቴሽንና ኢነርጂ ላይ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ መሆኑ ተገለጸ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሚኒስትሩ አማካሪ የሆኑት ዶ/ር ሚካኤል መሀሪ 13ኛ ባለድርሻ አካል ፎረም በተለያዩ ምክኒያቶች በቀኑ መደረግ አለመቻሉን ገልጸው 2ኛው የኢትዮጵያ ውሃና ኢነርጂ ሳምንት አውደ ርዕይ ላይ መደረጉ የተሻለ ልምድ ለመውሰድ መልካም አጋጣሚን የፈጠረ ነው ብለዋል።

Oct 2025

አውደ ርዕዩ የውሃና ኢነርጂ ዘርፉን ለማዘመን እየተሰራ ስለመሆኑ ማሳያ ነው።

አቶ መላኩ የከርሰምድር ውሃ ካርታ /ground water mapping/ ላይ የሚሰራው SUN WASH ፕሮጀክት ከዴንማርክ ያስገባውን titan machine የጂኦ-ፊዚክስ መሳሪያን በመጠቀም በጋምቤላ ክልል 8 መለስተኛ ጥልቅ የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ተሰርቶ ውጤታማ በመሆኑ ለሌሎች አጋር ድርጅቶች ለማስተዋወቅ ዕድል ፈጥሮልና

በባዘርኔት ፕሮጀክት አተገባበርና ውጤታማነት ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ።

የባዘርኔት ፕሮጀክት ብሔራዊ አስተባባሪ አቶ ሞላ ረዳ የአቅም ግንባታ ስልጠናው በአጠቃላይ የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር በዓለም ሀገራት የነበረውን ተሞክሮ በማየት በሀገራችን በተሻለና ውጥታማ በሚያደርግ መልኩ ለመተግበር ታስቦ ተዘጋጅቷል ብለዋል።

የውሃ ሀብቶቻችን በዘላቂነት ለመጠቀምና ለማስተዳር ውይይት ትብብርና የጋራ እርምጃ ያስፈልጋል ተባለ፡፡

በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ ውሃ የህልውናችንና የኢኮኖሚያችን መሰረት አሁን ላይ ደግሞ ለብልጽግና ፣ ለሰላምና ለልማት ወሳኝ የሆነ ስትራቴጂካዊ ሀብት ሆኖ ብቅ ማለቱን ጠቅሰው ሆኖም ግን በጣም ተጋላጭ ፣ አከራካሪ እና አለም አቀፍ ስጋቶችም ሁሉ በውሃ ላይ ትኩረት ማድረጋ

ከ2.72 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ለከርሰምድር ውሃ ሀብት አለኝታ ልየታ የሚውል የ49 ጥልቅ ጉድጔድ ቁፋሮ ዉል ስምምነት ተደረገ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ፕሮጀክቱ እንደ ተቋም ትልቅ ስኬት በመሆኑ የአካባቢውን ህብረተሰብ ከውሃ ጋር ተያይዞ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በዘላቂነት ለመመለስ አለኝታውን ቀድሞ ማወቅ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሠው ሥራው በተያዘለት የጊዜ ገደብ ጥራቱን ጠብቆ እንዲሰራና የማማከር ስራውን በሚገባ በማከናወ

ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት ኢነርጂ ወሣኝ መሆኑ ተገለፀ ።

ክቡር ዶ/ር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ በሀገራችን አብዛኛው የህብረተሠባችን ክፍል የባዮ ማስ ተጠቃሚ በመሆኑ የእፅዋቶች መጠን በከፍተኛ ሁኔታ እንዲቀነስ ፣የአየር ንብረት ለውጥ ፣የአፈር መሸርሸር ምክኒያት የግብርና ምርትና ምርታማነት በመቀነስ የምግብ ዋስትና እንዳናረጋግጥ ከማድረጉም በላይ በጭስ ምክኒያት ህብረተ

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጡ፡፡

ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ለህዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ም/ቤቶች የጋራ ስብሰባ ያደረጉትን የመክፈቻ ንግግር አስመልክቶ ከም/ቤቱ አባላት በሚቀርቡ ጥያቄዎች ላይ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ምላሽና ማብራሪያ ሰጡ፡፡

ኢትዮጵያ በውሃና ኢነርጂ ልማት ዘላቂነት ያለውና ለጋራ ብልፅግና መሪ ሚና እየተወጣች መሆኑ ተለጸ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በውሃና ኢነርጂ ሚኒሰቴር የተዘጋጀውን 2ኛውን የኢትዮጵያ የውሃ እና ኢነርጂ ሳምንት በሳይንስ ሙዚየም በመገኘት ከፍተው ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ 2ኛው የውሀና ኢነርጂ ሳምንት ሀገራችን በታዳሽ ኢነርጂ ፣ ኢትዮጵያ የውሃ ሃብት ጥበቃና አጠቃቀምን በተመለከተ ትርጉም ያ