Nov 2023

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እና በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መካከል የድርጊት መግባቢያ ስምምነት ተደረገ፡፡በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እና በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መካከል የድርጊት መግባቢያ ስምምነት ተደረገ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በስነ-ስርዓቱ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በቀጣይ ለምንሰራቸው ስራዎች የድርጊት መግባቢያ ስምምነት ስናደርግ የግድቤን በደጀ ኢኒሸቲቭ የሚፈጥረውን የስራ እድል መነሻ በማድረግ መሆኑን ገልጸው፤

በሩብ አመቱ ንፁህ የመጠጥ ውሃን ተደራሽ በማድረግ ውጤታማ ስራ መሰራቱ ተገለፀ።

ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከሚዲያ ጋር በነበራቸው ቆይታ በ2016 በጀት አመት በመጀመሪያው ሩብ አመት አፈፃፀም ላይ ንፁህ የመጠጥ ውሃን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በሚከናወኑ ተግባራት ጥሩ አፈፃፀም እንዳለ ገልፀው

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አመራሮች እና ሰራተኞች ከተጠሪ ተቋማት ጋር የፀረሙስና ቀንን አከበሩ፡፡

በሚኒስትር ዴኤታ ማእረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ ሙስና ለበርካታ ሀገራት ሠላም እና መረጋጋት ለማስከበር አደጋ እየሆና ውስብስብና ድንበር ተሻጋሪ መሆኑን ገልጸው፤ ይህ አፀያፊ ተግባር የጥቂቶችን ፍላጎት የሚያሟላ ቢሆንም ብዙሃንን የሚጎዳ እና በሀገር ሀብት ላይ ውድመት የሚያስከትል ብልሹ አሰ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከፓኪስታን ከፍተኛ የመንግስት ልኡካን ጋር በውሃና ኢነርጂ ዙሪያ ውይይት አደረገ፡፡

ልኡካን ቡድኑ ኢትዮጵያ በውሃ፣ በኢነርጂና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያላትን ልምድ ለመካፈል መምጣታቸውን ገልጸው፤ ሚኒስቴር መ/ቤቱ ኢነርጂን ከማመንጨት የሜመንጨት ሂደት ላይ፣ የውሃ ፖሊሲ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ፣ ታዳሽ ኢነርጂን በተመለከተ ያለው ተሞክሮን በተመለከተና የዋሃና ኢነርጂ ዘርፎች የአደረጃጀትና የሚመራበት ሂ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ እና ከዴንማርክ ኢምባሲ ጋር ተቋማዊ አቅም ግንባታ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሃግብር አካሄደ፡፡

በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሃይድሮሎጂና ተፋሰስ መረጃ መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ እንደተናገሩት፤ በአጋርነት የሚከናወኑ ሥራዎች በውሃ ሀብት አስተዳደር ላይ የላቀ ውጤት እንደሚያመጣ ገልፀዋል።

አገልግሎት መስጠት ከጀመረ አንድ አመት ያስቆጠረው የሶላር ኢነርጂ ማቀዝቀዣ ውጤታማ ነው ሲሉ ማህበራቱ ገለጹ፡፡

በሲዳማ ክልል ሸበዲኖ ወረዳ ለኩ ቀበሌ የተተከለው እና ለጣራሚሶና አካባቢ የአትክልትና ፍራፍሬ አምራችና አቅራቢ ማህበር የተላለፈው የአትክልትና ፍራፍሬ የሶላር ኢነርጂ ማቀዝቀዣ ፕሮጀክት ውጤታማ መሆኑ ተገለጸ ፡፡

Oct 2023

ከ 563 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የውሃ ተቋማት ቁሳቁሶች አቅርቦት ውል ተወሰደ፡፡

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ ስምምነቱ በድርቅና ጦርነት ለተጎዱ አካባቢዎች የተበላሹና አገልግሎት የማይሰጡ የውሃ ተቋማትን በመጠገን አስቸኳይ መፍትሔ ለመስጠት እጅግ ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡

ውሃ፣ ኢነርጂ እና መሬትን በማቀናጀት የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተጠቆመ ፡፡

ክቡር ዶ/ር ሱልጣን ወሊ እንደገለጹት የውሃ፣ ኢነርጂ እና የመሬት ትስስርን ለማቀድ፣ የሁኔታዎች እና የፖሊሲ ትንተና በማድረግ ለገጠሪቱ አፍሪካ ብሎም ለኢትዮጵያ ፍትሃዊ እድገት እንዲኖር አውደ ጥናቱ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡

የአንድ ቋት የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ብሄራዊ ፕሮግራም ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መሥራት ውጤት ማምጣት እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡

ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ ባለፉት ሶስት አመታት የአንድ ቋት ብሔራዊ የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮግራም ከፍተኛ በጀት ተመድቦለ ከፌዴራል እና ከክልሎች ጋር ተግባራዊ ለማድረግ ሰፊ ጥረት የተደረገ

በውሃ ፣ ሳኒቴሽንና ሀይጅን ዘርፍ ከ5 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያንን ተጠቃሚ የሚያደርግ የ5 ዓመት ስትራቴጅክ እቅድ ይፋ ተደረገ፡፡

ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ ሀገራችን ባስቀመጠችው የ10 ዓመት ስትራቴጅክ እቅድ መሰረት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በዚሁ ማዕቀፍ ስር እስከ 2030 ንጹህ የመጠጥ ውሃን ለሁሉም ዜጋ ተደራሽ ለማድረግ በሚደረገው ያለሰለሰ ጥረት እንደ ዋተር ኤድ ኢትዮጵያ ያሉ ድርጅቶች የሚያበረክቱት አስተዋጽኦ አስፈላጊና ጠቃሚ ነው ብ

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኩርሙክ ወረዳ የባለብዙ መንደር የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ፡፡

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ ሙሉ በሙሉ በመንግስት ወጪ የሚሸፈን ሆኖ የአካባቢው ማህበረሰብ በቅርበት የሚከታተለውና ድጋፍ የሚያደርግበት መሆኑን ገልጸው፤ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ እመንደሚጠናቀቅ ጠቁመዋል፡፡

Sep 2023

አገርአቀፍ የውሃና ኢነርጂ ኤግዚቢሽን መስከረም 10/2016 ዓ.ም ተጠናቋል።

በኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና በአረብ ኤምሬትስ ፕሬዚዳንት ክቡር ሸህ መሀመድ ቢን ዛይድ ነሐሴ 12/2015 ዓ.ም. በይፋ የተከፈተው አገርአቀፍ የውሃና ኢነርጂ ኤግዚቢሽን መስከረም 10/2016 ዓ.ም ተጠናቋል።

ተደጋግሞ ሊታይ የሚገባው አውደ ርዕይ ነው። ----- ዶ/ር ሙሉጌታ እንዳለ

የጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊው ዶ/ር ሙሉጌታ እንዳለ የውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር በየዘርፉ እየሰራቸው ያሉትን ስራዎች ለወጣቶች፣ለተማሪዎች እንዲሁም ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል አስተማሪ በሆነ መንገድ ተዘጋጅቶ የቀረበ አውደርዕይ

የነገው ትውልድ በውሃው ዘርፍ ተስፋ እንዳለው የሚያሳይ አውደርእይ ነው። ከጀርመን ፍራንክፈርት የመጡ ጎብኝ

የጀርመን ፍራንክፈርት ነዋሪው አውደርእዩን ለ2ኛ ጊዜ እንደጎበኙ ገልፀው የነገው ትውልድ ተስፋ እንዳለው የሚያሳይ በመሆኑ በኢትዮጵያ ውስጥ በዚህ ደረጃ የውሃ ሀብት መረጃ መደራጀቱ እንዳስደነቃቸው ገልጸዋል።

ከተጀመረ ወደ አንድ ወር የተጠጋው አውደርእይ በበርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተጎበኘ ነው፡፡

የውሀና ኢነርጅ ሚኒስቴር "የውሀ ሀብታችን ለብልጽግናችን" በሚል በሳይንስ ሙዚየም ለእይታ ከቀረበ ጀምሮ አምባሳደሮች፣ ሚንስትሮች፣ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የመጡ ሰዎችና የውጪ ዜጎች፣ የሚዲያ አካላት የጎበኙት ሲሆን

በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር የዱከም ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ሀገር አቀፍ ኤግዚቢሽን ጎበኙ።

የዱከም ክፍለ ከተማ ም/አስተዳዳሪ አቶ አዲስ ጌታቸው በቴክኖሎጂ የተደገፈ የሜቲዎሮሎጂ መረጃ አሰባሰብ እና አገልግሎት አሰጣጥ እውቀት ማግኘታቸውን ገልጸው፤ ያለንን የውሀ ሀብት ማወቅ እና ምን ያህል ጥቅም ላይ እንደዋለ ግንዛቤ አልነበረም

ከፍሳሽ አወጋገድ ጋር እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ጤናማ ህብረተሰብ ለመፍጠር ከሚያበረክተው አስተዋጽኦ ባሻገር የጽዳት ስራን እንደሚያቃልል ተገለጸ ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር የቂርቆስ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ስር የሚገኙ የጽዳት አስተዳደር ሰራተኞች በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀውን አገርአቀፍ የውሀና ኢነርጂ አውደ ርእይ ጎበኙ፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አመራሮች እና የማኔጅመንት አባላት አገርአቀፍ የውሃና ኢነርጂ ኤግዚቢሽንን ጎበኙ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጌትነት ታደሰ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እየተሰሩ ያሉ ፕሮጀክቶችና በዘርፉ እየተተገበሩ ያሉ ቴክኖሎጂዎች እንደሀገር ከፍተኛ ጠቀሜታ እዳላቸው ገልጸዋል።

የውሃ ወለድ በሽታዎችን በቅንጅት መከላከል እንደሚገባ ክቡር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ ገለፁ።

የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ሽፋን በከተማ እና በገጠር በአማካይ ከ60 - 70 በመቶ መድረሱን ገልፀው የሳኒቴሽን አገልግሎት በ2030 የዘላቂ የልማት ግቦችን እውን ለማድረግ የባለድርሻ አካላት ርብርብ እንደሚያስፈልግ

የንጹህ መጠጥ ውሀና ሳኒቴሽን አገልግሎት መጠናከር ለጤናው ዘርፍ ወሳኝ መሆኑ ተጠቆመ፡፡

ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ አውደርእዩ አስተማሪ እና እንደ ሀገር በውሀና ኢነርጂ ዘርፍ እየተሰሩ ያሉ ለኢኮኖሚያዊም ሆነ ለማህበራዊ እድገታችን ትልቅ ሚና ያላቸው በርካታ ስራዎች አይተናል ብለዋል፡፡

ውሃውም ኢነርጅውም የሁላችን ጉዳይ ስለሆነ አስተዋጿችን በምን መልኩ መሆን እንዳለበት የቤት ስራ የሰጠ አውደ ርዕይ።

ታዋቂውና ተወዳጁ አርቲስት ሚካኤል ታምሬ አገር አቀፍ የውሃና ኢነርጂ አውደርእይን ከጎበኘ በኋላ የተሰሩትንና ሊሰሩ የታሰቡትን ጭምር ማየት በመቻሌ ወደፊት ትልቅ ስራ እንደሚጠበቅብን አስገንዝቦኛል ብሏል።

የኦፍግሪድ፣ ባክ አፕና ሀይብሪድ አገልግሎቶችን ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እያደረገ የሚገኝ ድርጅት።

የካምፖኒው የኤሌክትሪክ ቴክኒሽያን አቶ የወንድወሰን እንዳለ እንደሚያስረዱት ካምፓኒው ሶስት አይነት አገልግሎቶችን የሚሰጥ ሲሆን ከዋናው የኤሌክትሪክ መስመር ውጭ ለሆኑ ገጠራማ አካባቢዎች የሶላር አማራጮችን በማቅረብ ማህበረሰቡ በተለይም ትምህርት ቤቶች፣ ጤና ጣቢያዎች፣ አብያተ ክርስቲያናት እንዲሁም ገዳማት የአገልግሎ

ከግሪድ ውጭ በርቀት የሚገኙ አካባቢዎችን ተደራሽ ለማድረግ ሚኒ ግሪዶችን ትግበራ በግሉ ዘርፍ ተሳትፎ እየተሰራ ነው ተባለ።

ክቡር ዶ/ር ሱልጣን ወሊ ባደረጉት ገለጻ፤ አብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ባለመሆኑ የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ኘሮግራም በመንደር ከግሪድና ከግሪድ ውጭ ባሉ ቴክኖሎዎች ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው፤

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአምራችነት ቀንን በተለያዩ ዝግጅቶች አከበረ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የተቋሙን ታሪካዊ አመሰራረት አስታውሰው መሪዎች በተለያየ ጊዜ ቢቀያየሩም የተቋም ግምባታ ሀገርን እንደሚያስቀጥል ጠቅሰው፤ ክቡር ሚኒስትሩ በዝግጅቱ ላይ ዘርፉ የውሃ ሀብት ክፍል በመባል በስራ ሚኒስቴር ሲቋቋም የስራ ሚንስትር የነበሩትን ራስ መንገሻ ስዩም ጨምሮ፤ ተቋሙን በቅብብሎሽ ለ

የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ሀላፊዎችና አባላት የውሃና ኢነርጂ አውደርዕይን ጎበኙ።

አቶ ተስፋሁን አሉላ የልደታ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ኃላፊ ሀገራችን በውሃው ዘርፍ ደመናን በማበልጸግ፣ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ስርአቱን ለማሻሻል እየተሰራ ያለው እንዲሁም የህዳሴ ግድባችን አሁናዊ ሁኔታ አገራችን በዘርፉ የደረሠችበትን ደረጃ ያሳየ አውደ ርዕይ ብለውታል።

የኢትዮጵያ የታዳሽ ኢነርጂ ልማት አየር ንብረት ለውጥ ኘሮግራም ጋር ተደጋጋፊ ነው።

ክቡር ዶ/ር ሱልጣን ወሊ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ተገኝተው እንደገለጹት የኢትዮጵያ የታዳሽ ኢነርጂ ልማት አየር ንብረት ለውጥ ኘሮግራም ያለውን ተደጋጋፊነትና ለሌሎች ዘርፎች እንደ ትራንስፖርት፣ ግብርናና ኢንዱስትሪ የመሳሰሉት የታዳሽ ኢነርጂ በመጠቀማቸው ለካርበን ልቀት ቅነሳ ትልቅ አ

የሳይንስ ሙዚየሙ የተቋማት ስራ ጎልቶ እንዲወጣ መንገድ ከፍቷል ተባለ፡፡

አውደርእዩ ላይ የተገኙት የኦሮሚያ ውሀና ኢነርጂ ቢሮ ኃላፊ ኢ/ር ሚሊዮን በቀለ ይህ የሳይንስ ሙዚየም መገንባቱ ተቋማት ስራዎቻቸው ጎልተው እንዲወጡ፤ በተለይ እንደ ውሀና ኢነርጂ ያሉ በቴክኖሎጂ የተደገፉ በርካታ ስራዎችን እየተሰሩ መሆኑ ህብረተሰቡ እንዲያውቅና የልማቱ አጋዥ እንዲሆን ትልቅ የሆነ አበርክቶ አለው ብለ

የውሃና ኢነርጂ ስራዎች ሳይንሳዊ ሆነው እንዴት ተሰንደው እንደቀረቡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ትምህርት የሚቀስምበት አውደ ርዕይ ነው፡፡

ክቡር አምባሳደር መለሰ አለም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃልአቀባዩ በነበራቸው ጉብኝት በሰጡት አስተያየት የበርካታ ሴክተሮች ትልቅ ችግር የሆነው ታሪካዊ ክንውኖችን ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በሚገባ ሰንዶ ለትውልድ ማስተላለፍ መሆኑን ጠቁመው፤

የኢነርጂ ልማት ለኢንዱስትሪ መስፋፋት ወሳኝ ነው ተባለ፡፡

የኢንደስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ታረቀኝ ቡልልታ በጉብኝታቸው ወቅት ሀገራችን ላይ ብዙ ያልተጠቀምንባቸው ሀብቶች እንዳላት እና አሁን ላይ የውሀ ሀብታችንን በአግባቡ ተጠቅመን መበልጸግ የምንችልበትን የእድገት ጎዳና ላይ መሆናችችን ያየንበት አውደርእይ ነው ብለዋል፡፡

የቀድሞ የውሃ ልማት ሚኒስትር የነበሩት ክቡር አምባሳደር ሽፈራው ጃርሶ የውሃና ኢነርጂ አውደርዕን ጎበኙ።

ክቡር አምባሳደሩ ከጉብኝት በኋላ በሰጡን አስተያየት የአሁኑ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በ1988ዓ.ም የውሃ ልማት ሚኒስቴር ሆኖ ሲቋቋም የመጀመሪያው ሚኒስትር ሆነው እንዳገለገሉ አስታውሰው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዛሬ ላይ በዚህ ደረጃ ደርሶ በማየታቸው በጣም መደሰታቸውን ገልጸዋል።

ፀሐይ ባለበት ሁሉ ለምግብ ማብሰያ አገልግሎት የሚውል የሶላር ቴክኖሎጂ በሳንይስ ሙዚየም ለእይታ ቀርቧል።

የሊደትኮ ኃ/የተ/የግል ማህበር የማርኬቲንግ ዳይሬክተር ወ/ሮ የምስራች ዜና ድርጅታቸው በኢትዮጵያ በተለያዩ አከባቢዎች ለ25 ዓመታት ልምድ ያካበተ መሆኑን ገልፀው በፀሐይ የሚሰሩ የውሃ ፓምፕ፣ ማሞቂያ እና የምግብ ማብሰያ ቴክኖሎጂዎችን ከዲዛይን ጀምሮ እስከ መገጣጠም ሥራ በራሱ አቅም ይሰራል ብለዋል።

በሳውዲ አረቢያ አምባሳደር የተመራ ልዑክ በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀውን አገርአቀፍ የውሃና ኢነርጂ ኤግዚቢሽን ጎበኙ።

አምባሳደሩ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀው አገርአቀፍ የውሃና ኢነርጂ ኤግዚቢሽን ኢትዮጵያ በዘርፉ በእድገት ጎዳና ላይ መሆኗን የሚያሳይ መሆኑን ገልጸው፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በአየር ንብረት እና በውሀ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት የሚመሰገን ነው

ሀገራዊ የተቀናጀ የውሀ ሀብት አስተዳደር ፕሮግራም ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ተካሄደ፡፡

የዘርፉ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ደበበ ደፈርሶ እንደነገሩን ፕሮግራሙን ማቋቋም ያስፈለገበት ዋና አላማ በውሃ ሀብት ላይ ፍላጎት ያላቸው አካላት በተበታተነ መንገድ ሲያፈሱት የነበረውን ሀብት፣ ጊዜ እና እቅዳቸውን በመሰብሰብ ወደ አንድ አምጥቶ በተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር ፕሮግራም እንዲመራ አስተዋጽኦ የሚያደርጉበት