Apr 2026

ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የፀሓይ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ዛሬ ያሰመረቅነው ፕሮጀክት ከ400 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት እና ከ6ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን የኤሌክትሪክ ሀይል ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የውሃ ፍቃድ አሰጣጥ ስርዓቱን ለማዘመን የሚያስችል የቴክኒካል አቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ ስልጠናውን በይፋ ሲያስጀምሩ ለውሃ ፈቃድ አሰጣጥ የe-Service ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ወሳኝ ሲሆን፤ ባህላዊና በወረቀት ላይ የተመሰረተ የውሃ ፍቃድ አሰጣጥን ወደ ዘመናዊ፣ ቀልጣፋ እና ግልፀኝነት ያለው ዲጂታል የአሰራር ስ

ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የጸሀይ ሀይል ማመንጫ ፕሮጀክት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በጋሞ ዞን ጋርዳማርታ ወረዳ የጎግሌ የጸሀይ ሀይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከ500 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተገነባና 6500 በላይ ቤተሰቦችን የሀይል ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል።

ከ1500 በላይ ቤተሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የጸሀይ ሀይል ማመንጫ ፕሮጀክት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ የፕሮጀክቱን ስራ መጀመር አስመልክቶ ባደረጉት ንግግር በካፋ ዞን አዲዮ ወረዳ መጫ ቀበሌ ከ150 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተገነባና ከ1500 በላይ ቤተሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ብለዋል።

የውሃ ሀብትን በሚፈለገው ልክ ጥቅም ላይ ለማዋል በዕቅድ መመራት ያስፈልጋል ተባለ።

የውሃ ሀብት መረጃን ለማስተዳደርና ለማጋራት የሚያስችል ረቂቅ መመሪያ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሲካሄድ የነበረው የውይይት ማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ የውሃ ሀብትን በሚፈለገው ልክ ጥቅም ላይ ለማዋል በዕቅድ መመራት እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ።

የውሃ ሃብት መረጃን ለማስተዳደርና ለማጋራት በሚያስችል ረቂቅ መመሪያ ላይ የምክክር አውደ ጥናት ተካሄደ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የውሃ ሀብት አስተዳደር በተቋሙ ላሉ ለመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን እና ለኢነርጂው ዘርፍ ወሳኝ በመሆኑ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብና ኮይሻ ለመሳሰሉት ትላልቅ ግድቦች የውሃ ሀብት መረጃ ወሳኝ ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ እያደገ በመጣው የኢነርጂ ልማት ዘርፍ ዓለም አቀፍ የግል ሴክተሩ ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆን ጥሪ ቀረበ፡፡

በኢትዮጵያ እያደገ በመጣው የኢነርጂ ልማት ዓለም አቀፍ የግል አልሚዎች ከመንግስት ጎን በመቆም የልማቱ ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ ያስተላለፉት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ ናቸው፡፡

የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የተዘጋጁ ሰነዶች በአብይ ኮሚቴ ተገመገሙ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የሪፎርሙ ዋና አላማ የተበታተኑ ስራዎችን መሰብሰብ በመሆኑ አሁንም እየተሰሩ ባሉ የዶክመንት ዝግጅት ስራዎች መበታተንና መስፋት እንዳይኖርና ተግባሮችን ስናስቀምጥ ከሌሎች ጋር ተመሳሳይ እንዳይሆኑ በሚገባ ማጤን ያስፈልጋል ብለዋል።

የከተሞችን የሳኒቴሽን ደረጃ ለማሻሻል የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ።

በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሳኒቴሽን መሠረተ ልማት መሪ ስራአስፈጻሚ የከተሞችን የሳኒቴሽን ደረጃ ለማሻሻል የሚያግዝ "operation & maintenance of treatmental plant" በሚል ርዕስ ለተመረጡ የክልል የውሃ ቢሮዎች እና ለከተማ የመጠጥ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎች ሀላፊዎችና ባለሙያዎች የአቅም ግ

ኢትዮጵያ እና ጎረቤቶቿ የጋራ ውሃን ወደ ጋራ ብልፅግና ለመለወጥ በሚያስችል መልኩ ውይይት ተደረገ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት፣ ከአፍሪካ ሀገራት የውሃ ሚኒስትሮች፣ ከናይል ተፋሰስ ኢኒሼቲቭ (NBI) ሀገራት የተውጣጡ እና ከፍተኛ የአካዳሚክ ተመራማሪዎች በተገኙበት ኢትዮጵያ እና ጎረቤቶቿ የጋራ ውሃን ወደ የጋራ ብልፅግና እንዴት መለወጥ እንደሚችሉ ተወያይተዋል።

በሻሸመኔ ከተማ በሳኒቴሽን መሠረተ ልማት ዘርፍ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ተጎበኙ።

የተጎበኙት ፕሮጀክቶች በ4.5 ሄክታር መሬት ላይ እየተገነባ ያለውን የሻሸመኔ ከተማ ዘመናዊ የፈሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያ Faecal sludge treatment plant/ ፕሮጀክት ጨምሮ የህዝብና የጋራ መፀዳጃ ቤቶች፣ከጋራ መኖሪያ ቤቶች መፀዳጃ ቤቶች ዙሪያ የተገነባ ሰው ሰራሽ እርጥበታማ ቦታዎች /wetland/ ናቸው።

ፕሮጀክቶችን በዘመናዊ መንገድ ክትትልና ግምገማ ለማድረግ የሚያስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከአለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ውጤታማ የጎርፍ በመከላከል ስራዎችን ሲሰራ የቆየ ሲሆን ስራውን በዘመናዊ መንገድ እንዴት ክትትልና ግምገማ ማድረግ እንደሚቻል በአለም ባንክ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።

የድንበር ተሻጋሪ ውሃን ጉዳይ በሚመለከት የተካሄዱ ጥናቶች ዓላማ፣ግኝት፣ ማጠቃለያና የመፍትሄ ሀሳቦች ዙሪያ ውይይት ተደረገ፡፡

የሱሉልታ ውሃና የውሃ ዲፕሎማሲ ኮንፈረንስ ላይ የተለያዩ ጥናቶች በዘርፉ ምሁራንና አጥኚዎች ተጠንተው ተሳታፊዎች ተከፋፍለው በተመደቡባቸው ክፍሎች የቀረቡ ሲሆን በአንደኛው ምድብ የድንበር ተሻጋሪ ውሃን ጉዳይ በሚመለከት የተካሄዱ ጥናቶች ዓላማ፣ግኝት፣ ማጠቃለያና የመፍትሄ ሀሳቦች ዙሪያ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

የከተማ ፈሳሽ ቆሻሻ አወጋገድን በዘመናዊ መንገድ ለማስተዳደር የሚያስችል ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የከተማ ፈሳሽ ቆሻሻ አወጋገድን በዘመናዊ መንገድ ለማስተዳደር የሚያስችል"Integrated waste water and septage management" በሚል ርዕስ ለተመረጡ የክልል ውሃ ቢሮና ለከተማ የውሃና ፈሳሽ አገልግሎት ሀላፊዎችና ባለሙያዎች ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

ባለፉት አራት ዓመታት በእጅጉ ስኬታማ የሆኑ የሀይድሮ ዲፕሎማሲ ስራዎች መሰራታቸውን ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ገለጹ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ባለፉት አራት ዓመታት በሀይድሮ ዲፕሎማሲ ስራችን ኢትዮጵያ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነቱን (CFA) ስድስት አገራት እንዲፈርሙ በማድረግ የቆየውን የቅኝ ግዛት አስተሳሰብ የቀየረ ታሪካዊ ድል ተቀዳጅታለች ብለዋል።

ለተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደር እውን መሆን አረንጓዴ አሻራ ወሳኝ ነው።

የተቀናጀ የውሃ ሀብት አስተዳደርን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ ወሳኝ ጉዳዮችን ለማየት የሚያስችል ኮንፈረንስ ነው ያሉት አቶ ደበበ ዘላቂ የውሃ ሀብት አስተዳደር ዕውን እንዲሆን በአረንጓዴ አሻራ ተፋሰስን (Catchment) የመጠበቅ ስራ አንዱና ዋነኛው ነው ብለዋል።

ሱሉልታ ውሃ እና ሃይድሮ ዲፕሎማሲ ኮንፈረንስ "የውሃ ዲፕሎማሲ እና ቀጠናዊ ትብብር ለዘላቂ ውሃና ኢነርጂ ልማትና አስተዳደር" በሚል መሪ ቃል እየተከበረ ነው።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ጋር በጋራ ባዘጋጀው ሱሉልታ ውሃ እና ሃይድሮ ዲፕሎማሲ ኮንፈረንስ "የውሃ ዲፕሎማሲ እና ቀጠናዊ ትብብር ለዘላቂ ውሃና ኢነርጂ ልማትና አስተዳደር" በሚል መሪ ቃል በቢሾፍቱ ከተማ እየተከበረ ነው።

አባይ የትብብር እንጂ የልዩነት ምንጭ አይደለም ሲሉ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ገለጹ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፉ በዓለም አቀፍ የሃይድሮ ዲፕሎማሲ ኮንፈረንስ እና በአባይ ተፋሰስ አገራት የቴክኒክ አማካሪ ኮሚቴ (TAC) ላይ ባደረጉት ይፋዊ የመክፈቻ ንግግር የናይል ተፋሰስ የጋራ ግንኙነት በፖለቲካዊ ሳይሆን በሳይንሳዊ እና በቴክኒካዊ መንገድ ሊመራ እንደሚገባ አሳስበዋል።

Mar 2026

የ88 የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች የግንባታና የቧንቧ ዝርጋታ የግዥ ሂደት ቅድመ ሁኔታ ላይ ከዘርፉ የግል ድርጅቶች ጋር ውይይት ተደረገ።

ክቡር ዶ/ር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በውሃ ሀብት አስተዳደር፣በመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍና በኢነርጂው ዘርፍ ባለፉት 5 ዓመታት ሰፊ ስራ ተሰርቶ ፣በሶስቱም ዘርፍ በርካታ ፕሮጀክቶች ተገንብተው ለአገልግሎት በማብቃት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በኢትዮጵያ የኬንያ አምባሳደርን በቢሯቸው አነጋገሩ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ አምባሳደሩ በጋራ ለመስራት ለውይይት በመምጣቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው፣ ኢትዮጵያ ከኬንያ ጋር ያላት ግንኙነት ታሪካዊ ብቻ ሳይሆን በደም የተሳሰረ ቤተሰባዊ ግንኙነት ያለው መሆኑን በአጵንኦት ገልጸዋል።

ጠንካራ ተቋማዊ አቅም ለመገንባት የሴቶችን እኩልነትና መብት መደገፍ ያስፈልጋል ተባለ፡፡

ጠንካራ ተቋማዊ አቅም ለመገንባት የሴቶችን እኩልነትና መብት መደገፍ ያስፈልጋል ሲሉ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሱልጣን ወሊ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ ጊዜ “Give to gain” በሃገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ “የሴቶች ድምጽ ለእኩልነት እና ለበለጸገች ኢትዮጵያ" በሚ

ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ግንባታ፣ ጥናት፣ ዲዛይንና ኤሌክትሮ መካናኒክ እቃዎች አቅርቦት ውል ስምምነት ተፈረመ።

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የህብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ በተገባው የውል ስምምነት መሰረት በሚፈለገው የጥራት ደረጃና በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ፕሮጀክቱን በማጠናቀቅ የህብረተሰቡ የመጠጥ ውሃ ችግር እንዲፈታ አሳስበዋል።

የመንግስት አስተዳደርና አደረጃጀት ማሳለጥ አምድ ላይ ውይይት ተደረገ።

የመንግስት አስተዳደርና አደረጃጀት ማሳለጥ አምድ ላይ መዋቅር ለማዘጋጀት የሚያስችል የስራ ፍሰት፣ የሚኒስቴር መ/ቤቱና የ3ቱ ተጠሪ ተቋማት የመዋቅር አደረጃጀት፣ የበፊቱን ውጤት መነሻ በማድረግ የቴክኒካል፣ የብቃትና የባህሪ ብቃት የተካተተበት የስራ መዘርዝር (Job description) እና ከጀማሪ እስከ ከፍተኛ ባለ

ልኡካን ቡደኑ በኢትዮጵያ ባካሄዱት ጉብኝት በተመለከቱት ለውጥ በእጅጉ መደመማቸውን ገለጹ፡፡

የዛምቤዚ የውሃ ተፋሰስ ኮሚሽን (zamcom) ከፍተኛ ልኡካን ኢትዮጵያ ከውሃ ጥበቃና ከተፋሰስ አስተዳደር ጋር በተገናኘ በምታካሂዳቸው ተግባራት ዙሪያ ልምድ ለመቅሰም ባካሄዱት ጉብኝት በእጅጉ መደመማቸውን ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ ለዛምቤዚ የውሃ ተፋሰስ ኮሚሽን ልኡካን በአረንጓዴ አሻራ ያላትን የካበተ ልምድ በስፋት እያካፈለች ነው።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ለልኡካኑ አስቀድመው የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉ ሲሆን ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ ያላት የውሃ ድርሻ 86 በመቶ እንደሆነና ይህንን በጋራ ለመጠቀም እንዲቻል ታችኞቹን የተፋሰስ ሀገራት ከግምት በማስገባት እያስተዳደረች መሆኑን አስገንዝበዋል።

በተቋሙ ለ 3ኛ ጊዜ የተካሄደው የረመዳን ወር የማፍጠር መርሃ ግብር የእስልምና እምነት የሚያዛቸውን ትዕዛዛት በተግባር ያሳየ መልካም ተግባር ነው ተባለ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ፣በሚኒስቴር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ፣ ከተቋሙ የተለያዩ የስራ ክፍሎች ስራ አስፈፃሚዎች፣ የተቋሙ ሙስሊም ማህበረሰብ እህቶችና ወንድሞች እንዲሁም ሌሎች ባለሙያዎች ናቸው።

የከርሰ ምድር ውሃ መረጃን በአግባቡ ማስተዳደር በሚል አጀንዳ የከፍተኛ ባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡

የብራይት ፕሮጀክት ማናጀር ዶ/ር ማማሩ አያሌው በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ እንደገለጹት ፕሮጀክቱ የተቀናጀ የውሃ ሃብት አስተዳደርን ለማስፈን በሚደረጉ ክንዋኔዎች በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በርካታ ስራ እየሰራ መሆኑን አውስተዋል፡፡በመሆኑም በእነዚህ ተፋሰሶች ዙሪያ የተቀናጀ የውሃ ሃብት አስተዳደር ተግባራትን

የገጠር የመጠጥ ውሃ አገልግሎት አቅርቦት ዘላቂ እና ምቹ እንዲሆን ለማድረግ አስቻይና ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው።

የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ዋና ሃላፊ ሚስተር ቪክተር ቫዝቄዝ ለተሳታፊዎች በበይነ መረብ በዋናነት ትኩረት አድርገው ካስተላለፉት ሃሳብ ለመገንዘብ እንደተቻለው በፕሮጀክቱ የተገነቡ የመጠጥ ውሃ ግንባታዎችን በዘላቂነት አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ ህብረተሰቡ፣የግል ድርጅቶች፣መንግስትና ሌ

የአንድ ቋት ብሄራዊ ዋሽ ፕሮግራም የሁለተኛው ፌዝ የስድስት ወር የፕሮጀክት አፈጻጸም ጥሩ ውጤት ማስመዝገቡ ተገለጸ፡፡

ክቡር ዶክተር አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ የአንድ ቋት ብሄራዊ ዋሽ ፕሮግራም የሁለተኛው ፌዝ ያለፈው የስድስት ወር ትልቅ ለውጥ ያመጣንበትና ሁሉም ፕሮጀክቶች ላይ ጠንካራ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ስራዎች ሁሉ ከ50 ፐርሰንት በላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያ በውሃ ሃብት ልማት በሰራችው ሰፊ ስራ በርካታ ለውጦች ተመዝግበዋል - ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት ኢትዮጵያ ከውሀ ጋር የተገናኙ ሠፊ አብዮታዊ ስራዎች በማከናወኗ በርካታ ለውጦች ተመዝገቧል፤ ሀገራችን ኢትዮጵያ የበርካታ የተፈጥሮ ሃብት ባለቤት ናት ከእነዚህ መካከል የከርሰ ምድር ውሃ ሃብት ትልቁ ጸጋ መሆኑን ጠቁመዋል።

የአቅም ግንባታ ስልጠናው በኢነርጂ ዘርፉ ሙያዊ እገዛ ለማድረግ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተሳታፊዎች ገለጹ።

በታዳሽ ኢነርጂ ተለዋዋጭ የትግበራ ዕቅድ ላይ ትኩረት አድርጎ በራማዳ ሆቴል ለአራት ቀናት የዘለቀው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በኢነርጂ ዘርፍ ለሚከናወኑ ተግባራት ሙያዊ እገዛ ለማድረግ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተሳታፊዎች ገለጹ።

ኢትየጵያ የኃይል ልማት ፍኖተ ካርታዋን (Ethiopia National Energy Compact) በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው ጉባኤ ላይ አቀረበች - የካቲት 26/2018 ዓ/ም

የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር የተከበሩ ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ በጉባኤው የከሰዓት በኋላ መድረክ ላይ የኢትዮጵያን የኃይል ልማት ፍኖተ ካርታ (Ethiopian National Energy Compact) አቅርበዋል፡፡

ድርቅን መቋቋም የሚችል ባለብዙ መንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት (CR wash) የስራ ነባራዊ ሁኔታ ግምገማ ተካሄደ፡፡

ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ሲሆኑ ድርቅን መቋቋም የሚችል ባለብዙ መንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት (climate resilient project) የዋን ዋሽ(one Wash) አንድ ቋት ፕሮግራም አንዱ ዘርፍ ሲሆን 34 በመቶ ሽፋን ተሰጥቶት ወደስራ የተገባበት ፕሮጀክት መሆኑን አመልክተው ከሁለት ወራት በ

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ የአፍሪካ ልማት ባንክ ልኡክን በቢሯቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ የአፍሪካ ልማት ባንክ ሉኡካኑን ባነጋገሩበት ወቅት ሚኒስቴር መ/ቤቱ አጋር ድርጅቶች ጋር እየተሰሩ ባሉ ፕሮግራሞች እና ፕሮጀክቶች ላይ ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

ለተቋሙ ሰራተኞች "ስነምግባራዊ ውሳኔና የጥቅም ግጭትን መከላከል እና ማስተዳደር" በሚል መሪ ሃሳብ ስልጠና ተሰጠ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን ትልልቅ ፕሮጀክቶችን የሚያስተዳድር በመሆኑ ከሰው ሀብት፣ ከፋይናንስና ከሎጀስቲክ አንፃር ስነምግባርን ተከትለን አገልግሎት መስጠት እንድንችል ስነምግባራዊ ውሳኔ እና የጥቅም ግጭት ምንነትን በአግባቡ ተረድተን እንዴት መከላከልና ማስተዳደር ይቻላል የሚለውን ግንዛ

ከ120 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ጥናት፣ዲዛይንና ግንባታ ክትትል ውል ስምምነት ተፈረመ።

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የህብረተሰቡን የመጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ በተገባው የውል ስምምነት መሰረት በሚፈለገው የጥራት ደረጃና በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ፕሮጀክቱን በማጠናቀቅ የህብረተሰቡ የመጠጥ ውሃ ችግር እንዲፈታ አሳስበዋል።

የብሔራዊ ዋን ዋሽ ፕሮግራም የሁለተኛው ምእራፍ የ6 ወራት አፈጻጸም እየተገመገመ ነው።

የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ የብሔራዊ ዋን ዋሽ ፕሮግራም የሁለተኛው ምእራፍ ማጠናቀቂያ ላይ እንደመሆናችን የተጀመሩትን ፕሮጀክቶች በውጤታማነት በመፈጸም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ትልቁ ትኩረት ሰጥተን የምንተገብረው ነው ብለዋል።

በኢነርጂ ልማት ዘርፍ በአግባቡ ያልተሰራ ዕቅድ ለሃይል እጥረት መከሰት ምክንያት ስለሚሆን ጥንቃቄ እንደሚሻ ተገለፀ።

ክቡር ዶ/ር ኢንጅነር ሱልጣን ወሊ በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ ከመጣው የሃገሪቱ የህዝብ ብዛትና የኢኮኖሚ ፍላጎት ጋር በተገናኘ በቂ የሆነ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ በሚከናወኑ ተግባራት ጥራት ያለው ዕቅድ ሁነኛ ሚና ስለሚጫወት በዘርፉ ለሚሰሩ ተግባራት በጥንቃቄ አቅዶ መመራት ያስፈልጋልም ብለዋል።

የጎርፍ ክስተትን በመከላከል ከተጋላጭነት ይልቅ ለዘላቂ ልማት ማዋል ይገባል ተባለ።

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ክቡር አቶ ሞቱማ መቃሳ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የውይይት መድረክ የማጠቃለያ መርሃ ግብር ላይ የጎርፍ ክስተትን በመከላከል ከተጋላጭነት ይልቅ ለዘላቂ ልማት ማዋል እንደሚገባ ገለፁ።

"በአድዋ ድል ሉአላዊነታችንን እንዳስከበርን የምግብ ሉአላዊነታችንን ለማረጋገጥም መረባረብ ይጠበቅብናል!"_ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሃብታሙ ኢተፋ

በኢትዮጵያ ሉአላዊነት ጉዳይ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አርበኛ ነው ያሉት ክቡር ሚኒስትሩ የውሃ ሃብታችንና የኢነርጂ ልማታችን የሃገሪቱን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ሁነኛ ሚና ስለሚጫወት በዘርፉ ተግተን ልንሰራ ይገባናል ብለዋል።

በጣሪያ የፀሐይ ኃይል ልማት ብሔራዊ መመሪያ ላይ ውይይት ተደረገ።

የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዲኤታ ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ውይይቱ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውና ከፍተኛ ጠቀሜታ ባለው የጣሪያ የፀሐይ ኃይል ልማት እና አጠቃቀም ብሔራዊ ሰነድ ላይ ለመወያየት እና ለማጥራት ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች እና የኦሞ ጊቤ ቤዚን የጎርፍ ተጋላጭነት ቅነሳ የቅድመ ጥናት ሪፖርት ላይ ውይይት እየተካሄደ ነው።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ከዚህ ቀደም የአዋሽ ቤዚን የጎርፍ ተጋላጭነት ቅነሳ ቅድመ ጥናት ሪፖርት ላይ ውይይት መደረጉን አስታውሰው፤ ጥናቱ የህብረተሰቡን የጎርፍ ተጋላጭነት ለመቀነስ በማን፣ ምንና መቼ ይተገበራል የሚለውንም የሚመልስና በሙያዊ ስነምግባር ሊተገበር የሚገባ መሆን እንዳለበት ጠቁመዋል።

ከ571 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚገነባው የአለታ ጩኮ ወረዳ የባለብዙ መንደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት አፈፃፀሙ ከ80 በመቶ በላይ ነው ተባለ።

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከ80 ሺህ በላይ ህዝብ ተጠቃሚ ያደርጋል ያሉት የአለታ ጩኮ ከተማ ከንቲባ አቶ ቶርባ ቶሼ በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢዎችና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች የመስክ ምልከታ ላይ ተገኝተው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተ

ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ፣ ጥራትና በጀት ጀምሮ የመጨረስ አቅም የታየበት መሆኑን ቋሚ ኮሚቴው ገለፀ።

የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢዎችና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከለጋሽ ድርጅቶች ጋር በጋራ በሲዳማ ክልል ዙሪያ የተሰሩ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶችን ያሉበትን ደረጃ የመስክ ምልከታ ግብረመልስ በሰጡበት ወቅት ከክልሉ ጋር በጋራ የተሰሩት የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ፣ ጥራትና በጀ

"የከፍተኛ አመራሩ አርአያነት ለጸረ ሙስና ትግል" በሚል መሪ ቃል ለውሃና ኢነርጂ ዘርፍ አመራሮች ስልጠና ተሰጠ።

ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ የዛሬው የስልጠና መድረክ ዋና ዓላማ የስራ ሀላፊዎችና ሰራተኞች ለዜጎች አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት ከሀላፊነታቸው ጋር በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ መንገድ የጥቅም ግጭት ውስጥ ሊከታቸው የሚችሉ ሁኔታዎች ሲያጋጥሟቸው ግጭቱን መከላከል ወይንም በአግባቡ ማስተዳደር እንዲችሉና ሙስናን መከላከ