ለኤረር CR-WASH ፕሮጀክት 48.7 ሚሊዮን ብር የአዋጭነት ጥናት፣ ዝርዝር ዲዛይንና የተግባር ስልጠና ውል ተፈረመ፡፡
በሱማሌ ክልል ለሚተገበረው የኤረር የአየር ንብረትን የሚቋቋም (Climate Resilient) የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን (CR-WASH) ፕሮጀክት ለማሳካት የሚያግዝ 48.7 ሚሊዮን ብር የአማካሪ አገልግሎት ውል በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት መካከል ተፈርሟል።