የውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት፣ ከክልል ውሀና ኢነርጂ ቢሮዎችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የ2015 ዓ.ም. በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ መካሄድ ተጀመረ፡፡
ነሀሴ 19/2015(ውኢሚ) መርሃ ግብሩ በሳይንስ ሙዚየም የተጀመረ ሲሆን በመርሀ ግብሩ ላይ የሚንስቴር መስሪያ ቤቱ እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የውሀ መስኖ ቆላማ አካባቢ እና አካባቢ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ የክልል ውሀና ኢነርጂ ቢሮ አመራሮች፤ እንዲሁም ባለድርሻ አካላትና አማካሪዎች ይሚሳተፋ ሲሆን መርሃግብሩ ለተከታታይ 4 ቀን የሚቀጥል ይሆናል፡፡